በሰባ ሁለት ዓመታት በረራዋ ከDouglas DC-3 ጢያራነት እጅጉን ዘመነኛ የሆነው Airbus A350-900 ጨምራ የ100 አውሮፕላኖች ባለቤት በመሆን ከአፍሪካ አቻ የለሽ አየር መንገድ ለመሆን በቅታለች።


የኢትዮጵያ - በመንገደኞች የበረራ አገልግሎት ብቻ የተወሰነች ባለመሆኗም ከጥገና እስከ ዕቃ ማጓጓዣ ግልጋሎቶችን ትሰጣለች።


ከራሷም አልፋ የባሕር ማዶኛ የበረራና አስተናጋጆችንንና አብራሪዎችን ሳይቀር በአካዳሚዋ አሰልጥና ለአየር ታበቃለች።

አቶ ኢሳያስ ወልደማርያም ኃይሉ፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዓለም አቀፍ አገልግሎቶች ማኔጂንግ ዳይሬክተርም በአዲስ አበባ ዋና መስሪያ ቤታቸው ስኬትን ትህትና አላብሰው ያወጉን ይህንኑ ነው። የኢትዮጵያ አየር መንገድን የሰባ ሁለት ዓመታት ጉዞ፣ የአገር ምጣኔ ሐብታ ታዳጊነትዋን፣ የፓን አፍሪካኒዝም አስፋፊነቷን፣ ከሰሞነኛው አወዛጋቢው የከፊል ፕራይቬታይዜይሽን ጉዳይ ጋር አዛንቀው።

ከትልማቸውን ነቅሰውም አውስትራሊያን አካትቶ የአየር መንገዷ ክንፎች ወዴት ለመቅዘፍ እንደተሰናዱ ፍንጭ ሰጥተዋል።
ኢትዮጵያውያን አብዝተው የአየር መንገዱ ተጠቃሚዎች እንዲሆኑም ጋብዘዋል።

