ኢትዮጵያ ውስጥ የዝናቡ ወቅት እያበቃ ነው፤ የአደይ አበባ አበባዎችም እያበቡ ነው።
ጊዜው የለውጥ ነው።
ጊዜው የዕደሳ ነው።
የአውስትራሊያ ሌበር ፓርቲም በዚህ ማለፊያና እውነተኛ መንፈስ ነው የሚዘልቀው።
የእናንተ አዲስ ዓመት በወርኃ ሴፕተምበር ነው፤ ኢትዮጵያም ወደ 2012 ዓመተ ምህረት እየዘለቀች ነው።
የቀን መቁጠሪያችሁ በእውነተኛነት የኢትዮጵያን ዘመን ያሸመገለ ታላቅ ታሪክ የሚያንጸባርቅ ነው።
አያሌ ሌሎች አገራት በታሪክ ማዕበል ሲዋጡና በካቶሊክ ቤተክርስቲያን አገዛዝ የራሳቸውን የዘመን ቀመር ሲለውጡ፤ እናንት ግና የራሳችሁን የቀን መቁጠሪያ ጠብቃችሁ ቆይታችኋል።
የእናንት የዘመን መቁጠሪያ፤ ልክ እንደባሕላችሁ ሁሉ ጥንታዊነቱን የጠበቀ ነው።
ሁሉም ነገር እንዳለ አይቆምምና የቅርብ ዓመታቱን እንኳ ሳንነቅስ - ኢትዮጵያ በታላቅ ለውጦች ውስጥ አልፋለች።
ይሁንና አዲሱን ዓመት ስታከብሩ፤ ለሁሉም ኢትዮጵያውያን - ኦርቶዶክስ፣ ሙስሊም፣ ፔንቴኮስታልና ሌሎች የክርስቲያን ቡድናትን አክሎ በተስፋና በስምምነት አንድ ለመሆን ማለፊያ ጊዜ ነው።
ጊዜ በማይሽረው ብልኃት የተቀረውን ዓለም ልብ ለማሰኘት፤ በአንድ ላይ ስታብሩ ብርቱና መልካም ትሆናላችሁ።
ለሁሉም ኢትዮጵያውያን መልካም አዲስ ዓመትን እመኛለሁ።
አመሰግናለሁ።
አንቶኒ አልባኒዚ
የተቃዋሚ ቡድን መሪ

