We Are Amharas: Col. Demeke Zewdu

Colnel (retired) Demeke Zewdu Source: SBS Amharic and PD
ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ፤ የወልቃይትና ጠገዴን የማንነት ጥያቄ ከትግራይ ብሔራዊ ክልል መስተዳደር እስከ ኢፌዴሪ ፌዴሬሽን ምክር ቤት ድረስ ካቀረቡ የኮሚቴ አባላት መካከል አንዱ ናቸው። በሳቢያውም ሕይወታቸው ለአደጋ ተጋልጧል። ለእሥራትም ተዳርገውበታል። ከእሥር የወጡት በአዲሱ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አስተዳደር ነው። ስለምን የወልቃይትና ጠገዴን የማንነት ጥያቄ ይዘው እንደተነሱ፣ ዘርን ሳይሆን ስነልቦንና ታሪክን መሰረት ያደረገ የአማራ ማንነት ማቆም እንደሚያሻና ኢትዮጵያ ውስጥ ተከስቶ ያለውን ለውጥ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ሊጠብቀው እንደሚገባ ያሳስባሉ። ቃለ ምልልሳችን የተካሄደው በወርሃ መስከረም ጎንደር ከተማ ከሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው ነው።
Share




