“እኩልነትና ፍትኅዊነትን የሚያስከብር ፌደራላዊ አወቃቀር እስካልተመሠረተ ድረስ በአገራችን ሰላምና መረጋጋት ይኖራል ብሎ ኢሕአፓ አያምንም” - ኢሕአፓ

*** የኢትዮጵያ ሕዝብ አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ)

Konjit Berhan

Konjit Berhan, Leader of the Ethiopian People's Revolutionary Party Source: Supplied

የኢትዮጵያ ሕዝብ አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ) ታህሳስ 23, 2013 “ክፋትን ተላብሶ የተዘራው ዘር መርዛማ ፍሬውን አፍርቷል” ሲል ባወጣው መግለጫ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ነዋሪ ኢትዮጵያውያን ላይ “አሰቃቂና ዘግናኝ ግድያ ሲፈጸም በከፍተኛ ሃዘንና ቁጭት እየተመለከትን ነው” ብሏል።

አክሎም “ነገሩን የበለጠ አሳሳቢ የሚያደርገው፣ ከእልቂቱና ከማፈናቀሉ ጀርባ በተለያየ ደረጃ የሚገኙ የመንግሥት አካላት ለእልቂቱ ተባባሪና ዋና ዘዋሪ ሆነው መገኘታቸው ነው” ሲልም ገልጧል። 

አያይዞም “ለዚህ ሁሉ የዘር ፍጅት ምክንያት የሆነው ሕገ መንግሥቱና ዘርን መሠረት አድርጎ የተዋቀረው የፌደራል ሥርዓት መሆኑን ሁሉም የሚያውቀው እና ፀሐይ የሞቀው ሃቅ ነው፡፡ ስለሆነም የኢትዮጵያውያንን ይሁንታ ያገኘ ሕገ መንግሥትና ሁሉንም ዜጎች በመፈቃቀድ፣ በእኩልነትና በፍትኅዊነት መብታቸውን ሊያስክብር የሚችል ፌደራላዊ አወቃቀር እስካልተመሠረተ ድረስ፣ በአገራችን ውስጥ ሰላምና መረጋጋት ይኖራል ብሎ ኢሕአፓ አያምንም” የሕገ መንግሥት ማሻሻያ እርምጃን አስፈላጊነት አፅንዖት ሰጥቶ አሳስቧል።

ኢሕአፓ በመግለጫው ለኢትዮጵያ ትድግና የበኩሉን ለመወጣት ዝግጁ መሆኑን አስገንዝቦ ለኢትዮጵያውያን ጥሪውን ሲያቀርብም “ኢትዮጵያ እንደ ሀገር መቀጠሏን እንፈልጋለን የምንል ኢትዮጵያውያን ሁሉ ሳንውል ሳናድር ተሰባስበን በመመካከር ለአገራችንና ለዜጎቻችን ህልውና እንድረስላቸው በማለት ኢሕአፓ ዛሬም ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡ ኢሕአፓም የበኩሉን አስተዋፅኦ ለማበርከት ዝግጁነቱን ያረጋግጣል። የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አስቸኳይ ስብሰባ ጠርቶ በማወያየት እና የጋራ አቋም በመያዝ ትርጉም ያለዉ መልዕክት ለመንግሥት እንዲያስተላልፍ እንጠይቃለን” ብሏል።

 


Share

Published

By Kassahun Seboqa Negewo

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service