ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ ር አብይ አህመድ በውስጥ ጉዳያችን ላይ የውጭ ጣልቃ ገብነትን አንቀበልም አሉ

PM Abiy Ahmed

PM Abiy Ahmed Source: AAP

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ በውስጥ ጉዳያችን ላይ የውጭ ጣልቃ ገብነትን አንቀበልም አሉ ፡፡

 ኢትዮጵያ በታሪኳ ሁሉ ፈርጀ ብዙ የሆኑትን አለም አቀፍ ህጎችን እና ደንቦች ስታከብር መቆየቷን አስታውሰው በተመሳሳዩም ፤  ኢትዮጵያ ህግን እና ስርአትን በማስከበር ሂደት ውስጥ ባለችበት በአሁኑ ውቅት ፤ የአለም አቀፉ ማህበረስቡ ለመርዳት ያሳየውን ፍላጎት አድንቀዋል፡፡ ይሁንና አካሄዱ በተመለከተ በአለማቀፍ ህግ መሰርት እንዲከናውውን አሳስበዋል፡፡

በዚህም መሰርት የኢትዮጵያ መንግስት የእርዳታ ጥሪን እስኪያቀርብ ድረስ የአለም አቀፉ ማህበረስብ ከማንኛውም አይነት ጣልቃ ገብነት ታቅቦ መጠበቅ ይኖርበታል ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያ በአሁን ሰአት ያለባትን ችግር የአለም አቀፍ መርሆዎችን በተከተለ መልኩ ለመፍታት አቅሙ እንዳላትም አሳስበዋል ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ አያይዘውም ምንም እንኳ የአጋሮቻችንን ስጋት እና ምክር ከግምት ውስጥ ብናስገባም ፤ በውስጥ ጉዳያችን ላይ የውጭ ጣልቃ ገብነትን ግን ሙሉ በሙሉ አንቀበለውም ብለዋል ፡፡በስተመጨረሻም  “ ከበሬታን በተሞላው መልኩ የምናገረው ነገር ቢኖር ፤ የአለም አቀፉ ማህበረሰብ ካልታጋበዙት ከማንኛውም አይነት ህገ ወጥ ጣልቃ ገብነት እንዲቆጠቡ ፤ እንዲሁም መሰረታዊ የሆነውን ህግ እንዲያከብሩ ነው ፡፡” ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ ር አብይ አህመድ ዛሬ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ ባወጡት መልእክት ፡፡


Share

Published

Updated

Presented by Martha Tsegaw

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ ር አብይ አህመድ በውስጥ ጉዳያችን ላይ የውጭ ጣልቃ ገብነትን አንቀበልም አሉ | SBS Amharic