Watch FIFA World Cup 2026™

LIVE, FREE and EXCLUSIVE

አቶ ማሞ ምህረቱ የብሔራዊ ባንክ ገዢ ሆነው ተሾሙ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ፤ የአዲስ ተሿሚ ዕጩ ሚኒስትሮች ሹመት በተወካዮች ምክር ቤት ይሁንታ እንዲቸረው ጠየቁ፤ ለብሔራዊ ባንክ ገዢና በሚኒስትር ማዕረግ የፖሊሲ አማካሪዎች ሹመቶችን አፀደቁ።

Mammo 1.jpg

Mamo Mihretu, Governor of the National Bank of Ethiopia.

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ዛሬ ጥር 12 ቀን 2015 የሶስት ዕጩ ሚኒስትሮችን ማዕረግ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ፅድቅ እንዲቸረው ጠየቁ።

በዚህም መሠረት፤

1. ዶ/ር ዓለሙ ስሜ - የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር

2. ኢንጂነር ኃብታሙ ተገኝ - የማዕድን ሚኒስትር

3. ዶ/ር ግርማ አመንቴ - የግብርና ሚኒስትር ሆነው በዕጩነት ቀርበዋል።

ከጥር 10 ቀን 2015 አንስቶም የብሔራዊ ባንክ ገዢና በሚኒስትር ማዕረግ የፖሊሲ አማካሪ ሹመኞች ሹመቶቻቸው በጠቅላይ ሚኒስትሩ የፅድቅ ውሳኔ አግኝቷል።

1. አቶ ማሞ ምህረቱ - የብሔራዊ ባንክ ገዢ

2. ወ/ሮ አለምፀሐይ ጳውሎስ - የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ኃላፊና የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር

3. ዲያቆን ዳንኤል ክብረት - የማኅበራዊ ዘርፍ አማካሪ ሚኒስትር

4. አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ - የውጭ ፖሊሲ አማካሪ ሚኒስትር

5. አቶ መለሰ ዓለሙ - በሚኒስትር ማዕረግ የዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ የዘርፍ አስተባባሪ ሆነው ተሾመዋል።


1 min read

Published

By Stringer Report

Source: SBS


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now