ግራ ክንፈኛው ሉላ ዳ ሲልቫ የብራዚልን ፕሬዚደንታዊ ምርጫ አሸነፉ

በሶማሊያ መዲና ሞቃዲሾ መኪናዎች ውስጥ በተጠመዱ ፈንጂዎች ሳቢያ ከ100 በላይ ሕይወቶች ተቀጠፉ።

Luiz Inacio Lula da Silva was Brazil's president between 2003 and 2010.jpg

Luiz Inacio Lula da Silva was Brazil's president between 2003 and 2010. Credit: Daniel Munoz/VIEWpress


ግራ ክንፈኛው ሉላ ዳ ሲልቫ የቀኝ አክራሪ ተቀናቃኛቸውን የወቅቱን ፕሬዚደንት ጃይር ቦልሶናሮን ድል ነስተው የብራዚል ፕሬዚደንታዊ ምርጫ አሸናፊ ሆኑ።

የፕሬዚደንታዊ ምርጫ ድሉ በ2018 ዘብጥያ ለ19 ወራት ተጥለው ለነበሩት ሉላ አስደናቂ ውጤት ተብሏል።
ሉላ ለእሥር ተዳርገው የነበሩት በሙስና ተወንጅለው የነበረ ቢሆንም በጠቅላይ ፍርድ ቤት ውሳኔ ባለፈው ዓመት ነፃ ወጥተዋል።

ዳ ሲልቫ ቀደም ሲል ከ2003-2010 ብራዚልን በፕሬዚደንትነት መርተዋል።

የፕሬዚደንታዊው ምርጫ ውጤት ብራዚል ውስጥ ባለፉት አሠርት ዓመታት ታይቶ የማይታወቅ ፅንፈኛ ቀኝ አክራሪ ተብሎ ሲተች የነበረውን መንግሥት ለክስመት ዳርጓል።

ሶማሊያ

ሞቃዲሾን የናጠው የመኪና ላይ የተጠመደ ቦምብ ጥቃት ከ100 በላይ ሕይወቶችን ቀጥፏል።

የአካባቢው ፖሊስ እንዳመለከተው አንደኛው ጥቃት ያነጣጠረው በትምህርት ሚኒስቴር ላይ ሲሆን፤ የተቀሩት ሁለቱ የመንግሥት ቢሮዎች፣ ሆቴሎችና ምግብ ቤቶች ላይ ነው።  
A general view shows the scene of a car bomb explosion in Mogadishu, Somalia.jpg
A general view shows the scene of a car bomb explosion in Mogadishu, Somalia on October 29, 2022. Credit: Abukar Mohamed Muhudin/Anadolu Agency via Getty Images

እስካሁን ጥቃቱን አስመልክቶ ኃላፊነቱን የወሰደ ቡድን አልተደመጠም። 

Share

Published

Updated

By Kassahun Seboqa Negewo, NACA
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service
ግራ ክንፈኛው ሉላ ዳ ሲልቫ የብራዚልን ፕሬዚደንታዊ ምርጫ አሸነፉ | SBS Amharic