መንግሥት ሕወሓትን በጥቃት ሰንዛሪነትና የተኩስ አቁም ስምምነት አፍራሽነት ከሰሰ

ሕወሓት በኢትዮጵያ መንግሥት ወታደራዊ ጥቃት የተከፈተበት መሆኑን አመለከተ

A damaged tank stands on a road north of Mekele.jpg

A damaged tank stands on a road north of Mekele on February 26, 2021. Credit: EDUARDO SOTERAS/AFP via Getty Images

የኢትዮጵያ መንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት የሕወሓት ቡድን በምሥራቅ ግንባር በቢሶበር፣ በዞብልና በተኩለሽ አቅጣጫዎች ከለሊቱ 11 ሰዓት ጀምሮ ጥቃት መፈጸሙን ተከትሎ የመከላከያ እርምጃ መውሰድ መጀመሩን አስታወቋል። 

የኮሙኒኬሽን አገልግሎቱ ዛሬ ረቡዕ በሰጠው መግለጫ "በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሽብርተኝነት  የተፈረጀው ሕወሓት በመንግሥት የቀረበለትን የሰላም አማራጮች ወደ ጎን በመተው ዛሬ ለሊት ላይ የፈፀመው ጥቃት የተኩስ ማቆም ስምምነቱን በይፋ ያፈእሰ ነው" ብሏል።  
አያይዞም፤ "ሕወሓት አሁንም ትንኮሳውን የሚገፋበት ከሆነ መንግሥት አስፈላጊውን እርምጃ ለመውሰድ" ዝግጁ መሆኑን ጠቅሶ፤ "የኢትዮጵያ መንግሥት ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ሕወሓት እያደረገ የሚገኘውን የጦርነት ጉሰማ እንዲያቆም ግፊት እንዲያደርጉ ጠይቋል" ሲልም ገልጧል።

ሰሞኑን የኢትዮጵያ መንግሥት ጥቃት ሰንዝሮብኛል በማለት አሳውቆ የነበረው ሕወሓት አሁንም በደቡባዊ አቅጣጫ ወታደራዊ ጥቃት ተከፍቶብኛል ሲል በቃል አቀባዩ አቶ ጌታቸው ረዳ በኩል አስታውቋል። 
ይህ በእንዲህ እንዳለም፤ በአገር መከላከያ ሠራዊት የመከላከያ ኅብረት ዘመቻ ዋና መምሪያ የመከላከያ ኃይል ስምሪት ኃላፊ ሜጀር ጀኔራል ተስፋዬ አያሌው፤ በሱዳን አድርጎ የአየር ክልል በመጣስ በሁመራ ሰሜናዊ ክፍል በኩል ወደ ትግራይ አልፎ ለሕወሓት "የጦር መሳሪያ ሊያቀበል የነበረና ንብረትነቱ የማን እንደሆነነ ያልታወቀ አውፕላን" በኢትዮጵያ አየር ኃይል ከምሽቱ አራት ሰዓት ላይ ተመትቶ መውደቁን አስታውቀዋል።

Share

Published

Updated

By Stringer Report
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service
መንግሥት ሕወሓትን በጥቃት ሰንዛሪነትና የተኩስ አቁም ስምምነት አፍራሽነት ከሰሰ | SBS Amharic