አውስትራሊያ ዴንማርክን ረትታ ለጥሎ ማለፍ ውድድር አለፈች

ቱኒዚያ ፈረንሳይን ድል ነሳች

Socceroos fans in Qatar .jpg

Socceroos fans in Qatar celebrating the team's win over Denmark. Credit: Twitter / @Benlewismedia

የአውስትራሊያ ብሔራዊ እግር ኳስ ቡድን ሶኮሩስ ዴንማርክን 1 ለ 0 በመርታት ለቀጣዩ የፊፋ ዓለም ዋንጫ 2022 አለፈች።

አውስትራሊያ በቀጣይነት ከቡድን C አሸናፊዎች አርጀንቲና ወይም ሜክሲኮ ጋር ለጥሎ ማለፍ ውድድር ተጋጣሚነት ትቀርባለች።

አውስትራሊያ ቀደም ሲል በዓለም ዋንጫ ውድድር 16 ቡድናት ለሚፋለሙበት ጥሎ ማለፍ ያለፈችው በ2006 ከክሮኤሽያ ጋር በአቻ ውጤት ተለያይታ ነው።

የአውስትራሊያ ቡድን ደጋፊዎች ከንጋቱ 2am AEDT በሜልበርን ፌዴሬሽን አደባባይ ከትልቅ የፊልም ስክሪን ፊት ለፊት ታድመው ድጋፋቸው ገልጠዋል።
ሌሎችም በየቡና ቤቱ ተሰባስበው ድጋፋቸውን በሆታ ቸረዋል።
ኳታር ያሉ አውስትራሊያንም ሳዑዲ አረቢያ አርጀንቲናን ስትረታ እንዳደረገችው ጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልባኒዚንም ለአውስትራሊያውያን የአንድ ቀን አገር አቀፍ የሥራ ዕረፍት እንዲሰጡ ጠይቀዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለም፤
ቱኒዚያ ፈረንሳይን 1 ለ 0
አርጀንቲና ፖላንድን 2 ለ 0
ሜክሲኮ ሳዑዲ አረቢያን 2 ለ 1 አሸንፈዋል።


Share

Published

By NACA, Kassahun Seboqa Negewo
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service