የተመድ ዋና ፀሐፊ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይና የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሰብሳቢ ጋር አዲስ አበባ ላይ ተገናኙ

ከፌዴራል መንግሥቱና ከትግራይ ታጣቂዎች የተውጣጣ የጋራ ኮሚቴ የትግራይ ታጣቂዎች እንደምን ትጥቅ እንደሚፈቱ ሽሬ ላይ እየተመከረ መሆኑ ተገለጠ።

United Nations Secretary-General Antonio Guterres.jpg

United Nations Secretary-General Antonio Guterres. Credit: John Lamparski/Getty Images

የተባበሩት መንግሥታት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ አዲስ አበባ ላይ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድና ከአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሰብሳቢ ሙሳ ፋኪ ጋር ዛሬ ሐሙስ ሕዳር 22 ተገናኝተው ተነጋገሩ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከዋና ፀሐፊው ጋር ያደረጉትን ውይይት አስመልክተው "ውጤታማ" ሲሉ ገልጠውታል።

ትግራይ

ፕሪቶያ ደቡብ አፍሪካ የተካሔደውን የሰላም ድርድር ተከትሎ የትግራይ ታጣቂዎች ትጥቅ የሚፈቱበትን ዝርዝር ዕቅድ አስመልክቶ ሽሬ ላይ በባለ ሙያዎች የጋራ ኮሚቴ እየተመከረበት መሆኑን የኢፌዴሪ መንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ዛሬ ባወጣው መግለጫ አስታወቀ።

የባለ ሙያዎቹ የጋራ ኮሚቴ ከትናንት ኅዳር 21 ቀን ጀምሮ ሽሬ ላይ ሥራውን የጀመረ ሲሆን፤ የተውጣጣውም ከፌዴራል መንግሥቱና ከትግራይ ታጣቂዎች መሆኑ ተነግሯል።

የጋራ ኮሚቴው ዝርዝር ዕቅድ ትጥቅ የማስፈታት፣ ካምፕ የማስገባትና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ መሆኑም ተገልጧል።

ኮሚቴው በመጪዎቹ ጥቂት ቀናት ውስጥ የዝርዝር ዕቅድ ነደፋውን እንደሚያከናውን ይጠበቃል።




Share

Published

By Kassahun Seboqa Negewo
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service