SKIP TO MAIN CONTENT

ኦሮምኛን አክሎ የአራት ተጨማሪ ቋንቋዎች ስርጭት በSBS ኦዲዮ ለጀመር ነው

SBS በጥቅሉ ከ63 በላይ በሆኑ ቋንቋዎች የኦዲዮ ስርጭቱን ያከናውናል። በቅርቡ ይፋ በሆነው የሕዝብ ቆጠራ ውጤት መሠረት 5.6 ሚሊየን አውስትራሊያውያን ቤታቸው ውስጥ የሚነጋገሩት ከእንግሊዝኛ ውጪ በሆኑ ቋንቋዎች ነው።

SBS Amharic News Podcast World.jfif
SBS በጥቅሉ ከ63 በላይ በሆኑ ቋንቋዎች የኦዲዮ ስርጭቱን ያከናውናል። በቅርቡ ይፋ በሆነው የሕዝብ ቆጠራ ውጤት መሠረት 5.6 ሚሊየን አውስትራሊያውያን ቤታቸው ውስጥ የሚነጋገሩት ከእንግሊዝኛ ውጪ በሆኑ ቋንቋዎች ነው። Credit: SBS Amharic

1 min read

Published

By Kassahun Seboqa Negewo, NACA

Source: SBS


Skip to article content

SBS ኦዲዮ በስርጭቱ ላይ አራት ቋንቋዎችን ሊያክል ነው።

ታካይ ቋንቋዎቹ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚነገረው ኦሮምኛ፣ ቫኑዋቱና ማላይ የሚነገረው ቢስላም፣ ቲሞር-ሌስቴ እና ምዕራብ ቲሞር የሚነገረው ቴተም አዲስ ስርጭት የሚጀምሩ ሲሆን፤ በደቡብ እስያ ማኅበረሰብ ውስጥ ተጠቃሚነቱ እያደገ ያለው ቴሉጉ በፓንጃቢና ኔፓሊ ቡድኖች ስር ዳግም ተስፋፍቶ ለስርጭት ይቀርባል።

በተያያዥነትም አውስትራሊያ ውስጥ የዕለት ተዕለት ኑሮና ተዛማጅነትን ለማገዝ የደቡብ እስያ ማኅበረሰብ ወጣቶች ላይ ያተኮረ የእንግሊዝኛ ስርጭት የሚቀርብ ይሆናል።

እንዲሁም፤ የነባር ዜጎች ቋንቋዎች እንዳይጠፉ ለመታደግ ስርጭት ይካሔዳል።

SBS በጥቅሉ ከ63 በላይ በሆኑ ቋንቋዎች የኦዲዮ ስርጭቱን ያከናውናል።

በቅርቡ ይፋ በሆነው የሕዝብ ቆጠራ ውጤት መሠረት 5.6 ሚሊየን አውስትራሊያውያን ቤታቸው ውስጥ የሚነጋገሩት ከእንግሊዝኛ ውጪ በሆኑ ቋንቋዎች ነው።


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Stream now