ዛሬ ማክሰኞ ኖቬምበር 1 / ጥቅምት 22 በተካሔደው 162ኛው ዓመታዊ የፈረስ ውድድር የአምስት ዓመቱ ፈረስ ጎልድ ትሪፕ አሸናፊ ሆኗል።
የ3200 ሜትሮች ውድድሩን ጋልቦ በአንደኛነት የጨረሰው ፈረስ ጋላቢ ማርክ ዛህራ የውድድር ማብቂያ መስመሩን በፈረሱ ጋልቦ ሲያቋርጥ "የማይታመን" "እንዴት ያለ ቀን። አጠገቤ የተጠጋ እንኳ የለም" ብሏል።
በሌላም በኩል የእንሰሳት መብቶች ተሟጋቾች ባለፈው የፈረሰ ውድድር ዓመት 139 ፈረሶች ለሞት መዳረጋቸውን ዋቤ ነቅሰው የተቃውሞ ድምፆቻቸውን አሰምተዋል።
80 ሺህ ያህል የስፖርቱ አፍቃሪዎች በታደሙበት የሜልበርን ፍሌሚንግተን ዓመታዊ የፈርስ ግልቢያ እሽቅድምድም ዓመቱን ቆጥሮ የፋሽን ትዕይንት ቀርቧል።
በ60ኛው የማየር ፋሽን ትዕይንት ታዋቂ የአገር ውስጥና ዓለም አቀፍ ሞዴሎች በትዕይንቱ ተሳትፈዋል።

አለባበሷ የበርካቶች መነጋገሪያ ለመሆን የበቃውን ድምፃዊት ዴልታ ጉድረምን ጨምሮ በርካታ ታዋቂ ግለሰቦችም በየፊናቸው የፋሽን ታይታው ተሳታፊ ሆነዋል።

የእናት ተፈጥሮን ዝናብ የፈረስ እሽቅድድሙን ከመመልከት አይገታንም ያሉ ነበሩ።


