የሕዝበ ውሳኔው ቅድመ ዝግጅት ተጠናቋል-ምርጫ ቦርድ

በደቡብ ክልል ስድስት ዞኖችና አምስት ልዩ ወረዳዎች ሕዝበ ውሳኔ ለማካሄድ በዝግጅት ላይ ናቸው፡

An electoral officials carries polling booths at a distribution center.jpg

An electoral official carries polling booths at a distribution centre in Ethiopia, on June 20, 2021. Credit: EDUARDO SOTERAS/AFP via Getty Images

ሕዝበ-ውሳኔውንም በተሳካ መልኩ ለማከናወን በቂ ዝግጅት መደረጉን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታውቋል።

የቦርዱ ዋና ሰብሳቢ ብርቱካን ሚደቅሳ ÷በደቡብ ክልል ሥር የሚገኙ ስድስት ዞኖችና አምስት ልዩ ወረዳዎች ለሚካሄደው ሕዝበ-ውሳኔ ስኬታማ ክንውን በቦርዱ በኩል በቂ ዝግጅት ተደርጓል ብለዋል።

በምርጫ ሂደት የሚያጋጥሙ ጉድለቶች የሚሻሻሉበት እና አፋጣኝ እርማት የሚወሰድበት የአሰራር ሥርዓት መዘርጋቱንም ጨምረው ገልጸዋል።

በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦች ክልል ሥር የሚገኙና ህዝበ-ውሳኔ የሚካሄድባቸው ስድስት ዞኖች (ኮንሶ፣ ደቡብ ኦሞ፣ ወላይታ፣ ጋሞ፣ ጌዴኦ፣ ጎፋ) እና አምስት ልዩ ወረዳዎች (ቡርጂ፣ ባስኬቶ፣ አሌ፣ አማሮ፣ ደራሼ) ናቸው፡፡

የሕዝበ- ውሳኔው የድምፅ አሰጣጥ ጥር 29 ቀን 2015 ዓ.ም እንደሚከናወን ታውቋል፡፡

Share

Published

By Stringer Report
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service