Watch FIFA World Cup 2026™

LIVE, FREE and EXCLUSIVE

የሕዝበ ውሳኔው ቅድመ ዝግጅት ተጠናቋል-ምርጫ ቦርድ

በደቡብ ክልል ስድስት ዞኖችና አምስት ልዩ ወረዳዎች ሕዝበ ውሳኔ ለማካሄድ በዝግጅት ላይ ናቸው፡

An electoral officials carries polling booths at a distribution center.jpg

An electoral official carries polling booths at a distribution centre in Ethiopia, on June 20, 2021. Credit: EDUARDO SOTERAS/AFP via Getty Images

ሕዝበ-ውሳኔውንም በተሳካ መልኩ ለማከናወን በቂ ዝግጅት መደረጉን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታውቋል።

የቦርዱ ዋና ሰብሳቢ ብርቱካን ሚደቅሳ ÷በደቡብ ክልል ሥር የሚገኙ ስድስት ዞኖችና አምስት ልዩ ወረዳዎች ለሚካሄደው ሕዝበ-ውሳኔ ስኬታማ ክንውን በቦርዱ በኩል በቂ ዝግጅት ተደርጓል ብለዋል።

በምርጫ ሂደት የሚያጋጥሙ ጉድለቶች የሚሻሻሉበት እና አፋጣኝ እርማት የሚወሰድበት የአሰራር ሥርዓት መዘርጋቱንም ጨምረው ገልጸዋል።

በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦች ክልል ሥር የሚገኙና ህዝበ-ውሳኔ የሚካሄድባቸው ስድስት ዞኖች (ኮንሶ፣ ደቡብ ኦሞ፣ ወላይታ፣ ጋሞ፣ ጌዴኦ፣ ጎፋ) እና አምስት ልዩ ወረዳዎች (ቡርጂ፣ ባስኬቶ፣ አሌ፣ አማሮ፣ ደራሼ) ናቸው፡፡

የሕዝበ- ውሳኔው የድምፅ አሰጣጥ ጥር 29 ቀን 2015 ዓ.ም እንደሚከናወን ታውቋል፡፡


1 min read

Published

By Stringer Report

Source: SBS


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now