ቦላ ቲኑቡ አዲሱ የናይጄሪያ ፕሬዚደንት ሆነው ተመረጡ

ፕሬዚደንት ቲኑቡ በትረ ስልጣናቸውን ከጨበጡ በኋላ ለ220 ሚሊየን ናይጄሪያውያን ባሰሙት ንግግር የቀድሞው ፕሬዚደንት ሙሃመዱ ቡሃሪ መፍታት የተሳናቸውን ምጣኔ ሃብታዊና ማኅበራዊ ችግሮችን መፍታት ቀዳሚ ውጥናቸው መሆኑን ገልጠዋል።

Bola Tinubu.jpg

Ruling party candidate Bola Tinubu won Nigeria's highly disputed weekend election, electoral authorities said on Wednesday, securing the former Lagos governor the presidency of Africa's most populous democracy. Credit: KOLA SULAIMON/AFP via Getty Images

በስልጣን ቁንጮ መንበር አስቀማጭነት ብርቱ ተፅዕኖ እንዳላቸው የሚነገርላቸው ቦላ ቲኑቡ ፅኑ ፉክክር በታየበት ብሔራዊ ምርጫ አሸናፊ በመሆን የናይጄሪያ አዲሱ ፕሬዚደንት ሆነው ተመረጡ።

በምርጫው ወቅት 36 ፐርሰንት ድምፅ አሸናፊ በመሆናቸውም ከተቀናቃኞቻቸው ከቀድሞው ምክትል ፕሬዚደንትና ነጋዴ አቲኩ አኩባካር እና የቀድሞው የክፍለ አገር አስተዳዳሪ ፒተር ኦቢ ጋር ለዳግም ፕሬዚደንታዊ ምርጫ መቅረብን ማስወገድ ችለዋል።

ፕሬዚደንት ቲኑቡ በትረ ስልጣናቸውን ከጨበጡ በኋላ ለ220 ሚሊየን ናይጄሪያውያን ባሰሙት ንግግር የቀድሞው ፕሬዚደንት ሙሃመዱ ቡሃሪ መፍታት የተሳናቸውን ምጣኔ ሃብታዊና ማኅበራዊ ችግሮችን መፍታት ቀዳሚ ውጥናቸው መሆኑን ገልጠዋል።

አቶ ቲኑቡ በናይጄሪያ መዲና አቡጃ ንግግራቸውን ባስደመጡበት ወቅት የፕሬዚደንታዊ ዕውቅና ምስክር ወረቀት ተሰጥቷቸዋል።

በሌላ በኩል ከቲኑቡ ጋር በዕጩ ፕሬዚደንት ተፎካክረው የነበሩት አኩባካርና ኦቢ የምርጫው ድምፅ ውጤት ቴክኒካዊ የሂደት ሳንካ ያለው በመሆኑ ውጤቱ እንዲመረመር የሚሹ መሆኑን አስታውቀዋል።
 





Share

Published

By NACA, Kassahun Seboqa Negewo
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service