Watch FIFA World Cup 2026™

LIVE, FREE and EXCLUSIVE

ቦላ ቲኑቡ አዲሱ የናይጄሪያ ፕሬዚደንት ሆነው ተመረጡ

ፕሬዚደንት ቲኑቡ በትረ ስልጣናቸውን ከጨበጡ በኋላ ለ220 ሚሊየን ናይጄሪያውያን ባሰሙት ንግግር የቀድሞው ፕሬዚደንት ሙሃመዱ ቡሃሪ መፍታት የተሳናቸውን ምጣኔ ሃብታዊና ማኅበራዊ ችግሮችን መፍታት ቀዳሚ ውጥናቸው መሆኑን ገልጠዋል።

Bola Tinubu.jpg

Ruling party candidate Bola Tinubu won Nigeria's highly disputed weekend election, electoral authorities said on Wednesday, securing the former Lagos governor the presidency of Africa's most populous democracy. Credit: KOLA SULAIMON/AFP via Getty Images

በስልጣን ቁንጮ መንበር አስቀማጭነት ብርቱ ተፅዕኖ እንዳላቸው የሚነገርላቸው ቦላ ቲኑቡ ፅኑ ፉክክር በታየበት ብሔራዊ ምርጫ አሸናፊ በመሆን የናይጄሪያ አዲሱ ፕሬዚደንት ሆነው ተመረጡ።

በምርጫው ወቅት 36 ፐርሰንት ድምፅ አሸናፊ በመሆናቸውም ከተቀናቃኞቻቸው ከቀድሞው ምክትል ፕሬዚደንትና ነጋዴ አቲኩ አኩባካር እና የቀድሞው የክፍለ አገር አስተዳዳሪ ፒተር ኦቢ ጋር ለዳግም ፕሬዚደንታዊ ምርጫ መቅረብን ማስወገድ ችለዋል።

ፕሬዚደንት ቲኑቡ በትረ ስልጣናቸውን ከጨበጡ በኋላ ለ220 ሚሊየን ናይጄሪያውያን ባሰሙት ንግግር የቀድሞው ፕሬዚደንት ሙሃመዱ ቡሃሪ መፍታት የተሳናቸውን ምጣኔ ሃብታዊና ማኅበራዊ ችግሮችን መፍታት ቀዳሚ ውጥናቸው መሆኑን ገልጠዋል።

አቶ ቲኑቡ በናይጄሪያ መዲና አቡጃ ንግግራቸውን ባስደመጡበት ወቅት የፕሬዚደንታዊ ዕውቅና ምስክር ወረቀት ተሰጥቷቸዋል።

በሌላ በኩል ከቲኑቡ ጋር በዕጩ ፕሬዚደንት ተፎካክረው የነበሩት አኩባካርና ኦቢ የምርጫው ድምፅ ውጤት ቴክኒካዊ የሂደት ሳንካ ያለው በመሆኑ ውጤቱ እንዲመረመር የሚሹ መሆኑን አስታውቀዋል።

 


1 min read

Published

By NACA, Kassahun Seboqa Negewo

Source: SBS


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now