ከጥቂት ሰዓታት በኋላ የአፍሪካ ኅብረት ልዑክ ቡድን መሪ ኦባሳንጆ የሰላም ንግግሩን አስመልክተው ጋዜጣዊ መግለጫ ሊሰጡ ነው

በኢትዮጵያ መንግሥትና ሕወሓት መካከል ከማክሰኞ አንስቶ ሲካሔድ የነበረው የሰላም ንግግር መቋጨት የነበረበት ባለፈው እሑድ ቢሆንም እስከ ዛሬ ቀጥሎ ሰንብቷል።

Member of the African Union mediation team, Former Nigerian President Olusegun Obasanjo (2ndL.jpg

Member of the African Union mediation team, Former Nigerian President Olusegun Obasanjo (2ndL) is greeted as he arrives for the peace talks between the Ethiopian government and Tigrayan People's Liberation Front (TPLF) held at the Department of International Relations and Cooperation (DIRCO) headquarters in Pretoria on October 26, 2022. Credit: PHILL MAGAKOE/AFP via Getty Images

በኢትዮጵያ መንግሥትና ሕወሓት መካከል ተከስቶ ላለው ግጭት ዕልባት ለማበጀት ካለፈው ማክሰኞ ጀምሮ እየተካሔደ ያለው የሰላም ንግግር የደረሰበትን ደረጃና ቀጣይ ሂደት አስመልክቶ ከጥቂት ሰዓታት በኋላ ጋዜጣዊ መግለጫ እንደሚሰጥ የደቡብ አፍሪካ ዓለም አቀፍ ግንኙነትና ትብብር ሚኒስቴር ይፋ አደረገ።
ጋዜጣዊ መግለጫ የሚሰTeውም በአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ከፍተኛ የምሥራቅ አፍሪካ ልዑክ ተወካይ ኦሉሴንገን ኦባሳንጆ መሆኑ ተነግሯል።

የሰላም ንግግሩ የተካሔደው በኦባሳንጆ መሪነት፣ በቀድሞው የኬንያ ፕሬዚደንት ኡኹሩ ኬንያታና የደቡብ አፍሪካ የቀሞዋ ምክትል ፕሬዚደንት ፉምዚሌ ምላምቦ ንጉካ ረዳትነት ሲሆን፤ በተሳታፊነትና ታዛቢነትም የኢጋድ፣ ተመድና ዩናይትድ ስቴትስ ተወካዮች ተገኝተዋል።



Share

Published

By Kassahun Seboqa Negewo
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service
ከጥቂት ሰዓታት በኋላ የአፍሪካ ኅብረት ልዑክ ቡድን መሪ ኦባሳንጆ የሰላም ንግግሩን አስመልክተው ጋዜጣዊ መግለጫ ሊሰጡ ነው | SBS Amharic