ከጥቂት ሰዓታት በኋላ የአፍሪካ ኅብረት ልዑክ ቡድን መሪ ኦባሳንጆ የሰላም ንግግሩን አስመልክተው ጋዜጣዊ መግለጫ ሊሰጡ ነው

በኢትዮጵያ መንግሥትና ሕወሓት መካከል ከማክሰኞ አንስቶ ሲካሔድ የነበረው የሰላም ንግግር መቋጨት የነበረበት ባለፈው እሑድ ቢሆንም እስከ ዛሬ ቀጥሎ ሰንብቷል።

Member of the African Union mediation team, Former Nigerian President Olusegun Obasanjo (2ndL.jpg

Member of the African Union mediation team, Former Nigerian President Olusegun Obasanjo (2ndL) is greeted as he arrives for the peace talks between the Ethiopian government and Tigrayan People's Liberation Front (TPLF) held at the Department of International Relations and Cooperation (DIRCO) headquarters in Pretoria on October 26, 2022. Credit: PHILL MAGAKOE/AFP via Getty Images

በኢትዮጵያ መንግሥትና ሕወሓት መካከል ተከስቶ ላለው ግጭት ዕልባት ለማበጀት ካለፈው ማክሰኞ ጀምሮ እየተካሔደ ያለው የሰላም ንግግር የደረሰበትን ደረጃና ቀጣይ ሂደት አስመልክቶ ከጥቂት ሰዓታት በኋላ ጋዜጣዊ መግለጫ እንደሚሰጥ የደቡብ አፍሪካ ዓለም አቀፍ ግንኙነትና ትብብር ሚኒስቴር ይፋ አደረገ።

ጋዜጣዊ መግለጫ የሚሰTeውም በአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ከፍተኛ የምሥራቅ አፍሪካ ልዑክ ተወካይ ኦሉሴንገን ኦባሳንጆ መሆኑ ተነግሯል።

የሰላም ንግግሩ የተካሔደው በኦባሳንጆ መሪነት፣ በቀድሞው የኬንያ ፕሬዚደንት ኡኹሩ ኬንያታና የደቡብ አፍሪካ የቀሞዋ ምክትል ፕሬዚደንት ፉምዚሌ ምላምቦ ንጉካ ረዳትነት ሲሆን፤ በተሳታፊነትና ታዛቢነትም የኢጋድ፣ ተመድና ዩናይትድ ስቴትስ ተወካዮች ተገኝተዋል።


1 min read

Published

By Kassahun Seboqa Negewo

Source: SBS


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now