አውስትራሊያ በመንግሥታዊ የእጅ ስልኮችና ኮምፒዩተሮች ቲክቶክን መጠቀም እንዳይቻል ማዕቀብ ጣለች

የአውስትራሊያ ብሔራዊ ባንክ በወርሃዊ ስብሰባው የወለድ ጭማሪ ሳያደርግ ቀረ

TikTok.jpg

The US, Canada and others have banned government employees from having TikTok on work devices. Credit: AAP / Kiichiro Sato

የአውስትራሊያ ፌዴራል መንግሥት የማኅበራዊ ሚዲያ ኧፕ ቲክቶክ ከመንግሥት ስልኮችና ኮምፒዩተሮች እንዲነሳ ወሰነ።

ለጋራ ብልፅግና መንግሥቱ ውሳኔ አስባብ የሆነው በቲክቶክ በኩል የሚሰበሰቡ ዳታዎች ወደ ቻይና መንግሥት እጅ ይገቡ ይሆናል ከሚል የደህንነት ስጋት ጋር ተያይዞ ነው።

ሆኖም፤ የግሪንስ ፓርቲ የፌዴራል መንግሥቱ በቲክቶክ ላይ የጣለውን ዕቀባ በፖለቲካ ተውኔትነት ፈርጆታል።

የግሪንስ ዲጂታል መብቶች ቃል አቀባይ ዲቪድ ሹብሪጅ ቲክቶክ ላይ የተጣለው ዕቀባ ብርቱ የማሻሻያ እርምጃ እንዳልሆነ፣ የሳይበር ሴኩሪቲ ስጋት በእያንዳንዱ ማኅበራዊ ሚዲያ መድረክ ውስጥ እንዳለና የዳታ ጉዳዮችም አማዞን፣ ሜታና ፌስቡክንም እንደሚያካትት ጠቁመዋል።

ብሔራዊ ባንክ

የአውስትራሊያ ብሔራዊ ባንክ ዛሬ ማክሰኞ መጋቢት 26 / ኤፕሪል 4 ባካሔደው ወርሃዊ ስብሰባው የወለድ መጠን ላለመጨመር ውስኖ ተነስቷል።

ብሔራዊ ባንኩ ካለፈው ዓመት ወርኃ ሜይ አንስቶ በተከታታይ የወለድ መጠኖችን ሲጨምር ቆይቷል።

የብሔራዊ ባንኩ ገዢ ፊሊፕ ሎው ባወጡት መግለጫቸው የወለድ መጠኑ አሁን የሚገኝበት 3.60 ፐርሰንት ቀደም ሲል የተጨመሩ የወለድ መጠኖችን ተፅዕኖ ለመገምገም ጊዜ እንደሚሰጥ አመላክተዋል።

የፌዴራል መንግሥቱም በበኩሉ ብሔራዊ ባንኩ በዛሬ ወርሃዊ ስብሰባው ተጨማሪ የወለድ መጠን ላለመጨመር መወሰኑን በመልካም ጎኑ ተቀብሎታል።



 







Share

Published

Updated

By Kassahun Seboqa Negewo, NACA
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service