የዩናይትድ ስቴትስ ቡድን ለፊፋ ዓለም ዋንጫ ጥሎ ማለፍ ግጥሚያ ካለፉት 16 ቡድናት ውስጥ በኔዘርላንድስ 3 ለ 1 በመረታት ከዓለም ዋንጫ ውድድር የመጀመሪያው ተሰናባች ቡድን ሆኗል።
ለኔዘርላንድስ ግቦቹን ያስቆጠሩት ሜምፊስ ዲፔይ 10' ዴሊ ብላይንድ 45+1' እና ዴንዚል ዳምፍራይስ 81' ሲሆኑ፤ ሐጂ ራይት በ76ኛው ደቂቃ ለዩናይትድ ስቴትስ ብቸኛዋን ግብ አስቆጥሯል።
ኔዘርላንድስ በቀጣይነት ከአውስትራሊያና አርጀንቲና አሸናፊ ከሆነው ቡድን ጋር ቅዳሜ ዲሴምበር 10 ማለዳ 6፡00 am ለሩብ ፍፃሜ ውድድር ይጋጠማል።
አውስትራሊያ ውስጥ በየክፍለ አገራቱ ከትላልቅ የቲሌቪዥን ስክሪን የእግር ኳስ ደጋፊዎች ግጥሚያውን በቀጥታ እየተከታተሉ ነው።
የሜልበርን ፌዴሬሽን አደባባይ ለአውስትራሊያ ደጋፊዎች መመልከቻ ስለማይበቃ ተጨማሪ መመልከቻ ሥፍራ AAMI ፓርክ ላይ ተሰናድቶ በርካቶች ታድመው እየተመለከቱ ነው።
የአውስትራሊያና አርጀንቲና ጥሎ ማለፍ ግጥሚያ በመካሔድ ላይ ሲሆን፤ በመጀመሪያው አጋማሽ ጨዋታ አርጀንቲና በሊዮኔል ሚሲ አማካይነት በ35ኛው ደቂቃ ባስቆጠረችው ግብ አውስትራሊያን 1 ለ 0 እየመራች ነው።

Lionel Messi of Argentina celebrates after scoring the team's first goal during the FIFA World Cup Qatar 2022 Round of 16 match between Argentina and Australia at Ahmad Bin Ali Stadium on December 03, 2022 in Doha, Qatar. Credit: Francois Nel/Getty Images