የፔሌ የቀብር ሥነ ሥርዓት ተፈፀመ

በማሊ መዲና ባማኮ አምስት ሰዎች ባልታወቁ ታጣቂዎች በደረሰባቸው ጥቃት ሕይወታቸውን አጡ

The coffin of soccer legend Pele arrives at a Santos cemetery .jpg

The coffin of soccer legend Pele arrives at a Santos cemetery.

በእግር ኳስ ጥበቡ ከሕይወት በላይ ግዘፍ ነስቶ የነበረው የብራዚላዊው ፒሌ የቀብር ሥነ ሥር ዓት ተፈፀመ።

ፒሌ ከዚህ ዓለም በ82 ዓመቱ በሞት የተለየው ለአንድ ዓመት ያህል ከካንሰር ጋር ሲፋለም ቆይቶ ነው።

አዲሱን የብራዚል ፕሬዚደንት ሉላን ጨምሮ 230,000 ያህል ለቀስተኞች በሳንቶስ እግር ኳስ ክለብ ቪላ ቤልሚሮ ስታዲየም ተገኝተው አስከሬኑን ተሰናብተዋል።

ፕሬዚደንት ሉላ ከእንግዲህ የቀድሞ የእግር ኳስ ፊልሞቹን በማየት ካልሆነ በስተቀር ዳግም ላያዩት በስታዲየም ተገኝተው ለመጨረሻ ጊዜ መሰናበታቸው ያሳደረባቸውን ጥልቅ ሐዘን ገልጠዋል።

አክለውም፤ ጭፍን ጥላቻ እስካሁን ገንኖ ባለባት አገር ደሃ፣ ጥቁር ሆኖ ለተወለደው ሰው "ዓለም ክብርን የማላበስ ዕዳ አለባት" ብለዋል።

ማሊ

የማሊ የደኅንነት ሚኒስትር ባወጣው መግለጫ በመዲናይቱ ባማኮ አንድ የሲቪል መከላከል ተቋም ባለበት አቅራቢያ ባልታወቁ ሰዎች በተሰነዘሩ ጥቃቶች አምስት ሰዎች ሕይወታቸውን ማጣታቸውን ገለጠ።

የሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ መግለጫ ለጥቃቱ ተጠያቂ አድርጎ ያነሳው አካል የለም።

የማሊ ማዕከላዊና ሰሜናዊ ክፍለ አገራት በእስላማዊ አማፅያን ታውኮ ይገኛል።

ምንም እንኳ መግለጫው ዝርዝር ማብራሪያዎችን ባይሰጥም፤ በጥቃቱ ሕይወታቸውን ካጡት ግለሰቦች ውስጥ ሁለቱ የሲቪል መከላከል ኃይል አባላት ሲሆኑ፤ ሶስቱ ሰላማዊ ሰዎች እንደሆኑ አመልክቷል።

 





Share

Published

By Kassahun Seboqa Negewo, NACA
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service