የሞባይል ክፍያ ሥርዓት የኢትዮጵያን የአገር ዉስጥ ዕድገት በ5.3 ቢሊዮን ዶላር ሊጨምር ይችላል ተባለ

የአውስትራሊያ ብሔራዊ ባንክ የወለድ መጠን ባለበት 4.10 ፐርሰንት ላይ ረግቶ እንዲቆይ ወሰነ።

Ethio Telecom.jpg

Credit: Ethio Telecom

በኢትዮጵያ የሞባይል ክፍያ ሥርዓት በስፋት ጥቅም ላይ ከዋለ የአገር ዉስጥ እድገት (ጂዲፒ) 5 ነጥብ 3 ቢሊዮን ዶላር እንደሚጨምር ዓለም አቀፍ የሞባይል ግንኙነት ሥርዓት ማኅበር አስታወቀ።

 ይህም የሚሆነው በፈረንጆች 2030 ከአጠቃላይ የአገሪቱ ሕዝብ 60 በመቶ ያህሉ የሞባይል ክፍያ ሥርዓት ተጠቃሚ ከሆኑ ነው ያለው ማኅበሩ፤ በተጨማሪም 700 ሺሕ ሰዎችን ከአስከፊ ድህነት እንደሚያወጣና የታክስ ገቢን በ300 ሚሊዮን ዶላር እንደሚጨምር አመላክቷል፡፡

 ይሁን እንጂ በኢትዮጵያ በአንፃራዊነት 99 በመቶ የኔትዎርክ ሽፋን ተደራሽነት ቢኖርም፤ የኔትዎርክ ጥራት አስተማማኝ አለመሆን፣ የዲጂታል ስርዓቱ ግንዛቤ ጉድለት፣ የዕምነትና የመረጃ ግላዊነትና ደህንነት ጥያቄ እንዲሁም የግብይቶች በተደጋጋሚ መስተጓጎል የሞባይል ገንዘብ ክፍያን እና አጠቃቀም ላይ እንቅፋት እየሆነ እንደሚገኝ ተጠቅሷል።

 በተጨማሪም፤ በ2021 የኤሌክትሪክ ኃይል ያላቸው ኢትዮጵያውያን 51 በመቶው ብቻ በመሆናቸው ኤሌክትሪክም ሃይል አለመኖር ትልቅ ፈተና ነው ተብሏል።

ኢትዮጵያ በምስራቅ አፍሪካ ከሚገኙ ጎረቤቶቿ ጋር ሲነጻጸር የገንዘብ ክፍያ ሥርዓት ተሳትፎዋ በጣም ዝቅተኛ ነው የተባለ ሲሆን፤ በ2022 በኬኒያ ከ80 በመቶ በላይ፣ በሩዋንዳ 77 በመቶ፣ በኡጋንዳ 66 በመቶ የሚሆኑ ጎልማሶች የባንክ ወይም የሞባይል ገንዘብ መክፈያ አካውንት እንዳላቸው የተገኘው መረጃ ጠቁሟል።

የወለድ መጠን

የአውስትራሊያ ብሔራዊ ባንክ የወለድ መጠን ባለበት 4.10 ፐርሰንት ላይ ረግቶ እንዲቆይ ወሰነ።

ማዕከላዊ ባንኩ ካለፈው ወር ሜይ አንስቶ ያካሔዳቸው 12 የወለድ መጠን ጭማሪዎች "በምጣኔ ሃብቱ የአቅርቦትና ፍላጎት መካከል ያለው ሚዛን ይበልጡን ዘለቄታ እንዲኖረው" አዎንታዊ ተፅዕኖ ማሳደሩ ያረካው መሆኑን አመልክቷል።

 የባንኩ ቦርድ የወለድ መጠን ጭማሪን በእዚህ ወር የመግታት ውሳኔ የምጣኔ ሃብቱን ለመገምገም ተጨማሪ ጊዜ እንደሚሰጠው ጠቅሷል።

በማከልም፤ የአውስትራሊያ ዋጋ ግሽበት ለተወሰኑ ጊዜያት ከፍ ብሎ እንደሚቆይ ጠቁሟል።

ወርሃዊ የሸማቾች ዋጋ ሰንጠረዥ በወርሃ ሜይ ከ 6.8 ፐርሰንት ወደ 5.6 ፐርሰንት ዝቅ ብሏል።



Share

Published

Updated

By NACA, Kassahun Seboqa Negewo, Stringer Report
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service
የሞባይል ክፍያ ሥርዓት የኢትዮጵያን የአገር ዉስጥ ዕድገት በ5.3 ቢሊዮን ዶላር ሊጨምር ይችላል ተባለ | SBS Amharic