Watch FIFA World Cup 2026™

LIVE, FREE and EXCLUSIVE

በዓድዋ በዓል ላይ የጸጥታ ኃይሎች በፈጸሙት ድርጊት ተጠያቂ እንዲሆኑ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን ጠየቀ

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በ127ኛው የዓድዋ ድል በዓል ላይ በመንግሥት የጸጥታ አካላት የተፈጠረውን ችግር አስመለክቶ ባወጣው መግለጫ፣ የጸጥታ ኃይሎች ከገደብ ያለፈ ድርጊት ፈጽመዋል ብሏል፡፡

Daniel Bekele, Chief Commissioner of the Ethiopian Human Rights Commission (EHRC).jpg

Dr Daniel Bekele, Chief Commissioner of the Ethiopian Human Rights Commission (EHRC), Credit: EDUARDO SOTERAS/AFP via Getty Images

ኮሚሽኑ ለአዲስ ማለዳ በላከው መግለጫ፣ በበዓሉ ላይ አላስፈላጊ ኃይል የተጠቀሙ እና ከመጠን ያለፈ እርምጃ ወሰዱ የመንግሥት የጸጥታ ኃይሎ፣ በሕግ ተጠያቂ ከመሆናቸው በተጨማሪ በሕግ አስከባሪዎች መሰል አደጋዎች እንዳይከሰቱ አስፈላጊ ሥልጠና ማግኘት አለባቸው ብሏል፡፡

የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ዳንኤል በቀለ(ዶ/ር) በበዓሉ ላይ የተከሰቱትን ክስተቶች አስመልክተው በሰጡት ሀሳብ፣ የጸጥታ ኃይሎች በዓሉን ለማክበር በወጣው ሕዝብ ላይ ከልክ ያለፈ አላስፈላጊ ድብደባ፣ አስለቃሽ ጭስ፣ ጥይትና ሌሎች ከመጠን ያለፉ እምጃዎችን መውሰዳቸውን ጠቁመዋል፡፡

በተወሰደው እርምጃ በዕድሜ የገፉ አዛውንቶችና ህጻናት ሳይቀሩ ጉዳት ማስተናገዳቸውን ቢንስ አንድ ሰው መገደሉን ኮሚሽነሩ ተናግረዋል፡፡ በርካታ ሰዎች የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል ሲሊም ኮሚሽነሩ አክለዋል፡፡ በምኒልክ አደባባይ የዓድን ድል ለማክበር፣ እንዲሁም በአቅራቢያው በሚገኘው ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስትያን ሃይማኖታዊ በዓል ለማክበር የተሰበሰበው ሕዝባዊ በኃይል መበተኑን ኮሚሽነሩ ገልጸዋል፡፡

የሕዝብን ደህንነት ማስጠበቅ እና የኹሉንም ሰው ሰብአዊ መብቶች ማስከበር ቀዳሚ ኃላፊነቱ የሆነው፣ የጸጥታ ኃይል የሚወስዳቸው አላስፈላጊ እና ከመጠን ያለፉ እርምጃዎች በሕግ ሊጠየቁ እንደሚገባም ተጠቁሟል፡፡


1 min read

Published

By Stringer Report

Source: SBS


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now