Watch FIFA World Cup 2026™

LIVE, FREE and EXCLUSIVE

ዩናይትድ ስቴትስ ለትግራይ የምታደርገውን የምግብ እርዳታ መግታቷን አስታወቀች

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚደንት፤ የእርዳታ ምግብ ሽያጭን አስመልክቶ በከፍተኛ ደረጃ ምርመራ ማስጀመራቸውንና ዓለም አቀፍ የረድኤት ድርጅቶቹ ዘርፈ ብዙ ልግስናቸውን እንዳያስተጓጉሉ ጥሪ አቅርበዋል።

Samantha Power.jpg

Samantha Power, United States Agency for International Development (USAID) administrator. Credit: Leigh Vogel/UPI/Bloomberg via Getty Images

የዩናይትድ ስቴትስ ዓለም አቀፍ ልማት ኤጀንሲ አስተዳዳሪ ሳማንታ ፓወር ሜይ 3 ባወጡት መግለጫ ኤጄንሲው "የምግብ እርዳታውን ለትግራይ ክልል ለመግታት አዋኪ ውሳኔ ወስኗል" ሲሉ አስታወቀዋል።

መግለጫው፤ ኤጄንሲው ምንም እንኳ የወሰደው እርምጃ አዋኪ ቢሆንም፤ በረሃብ ለተጎዱ የትግራይ ሕዝብ አስቦ ያቀረበው የምግብ እርዳታ ወደ ገበያ ወጥቶ ለሽያጭ መቅረቡ ችሮታውን ለመግታት ግድ እንዳሰኘው ገልጧል።

አክሎም፤ የዩናይትድ ስቴትስ ዓለም አቀፍ ልማት ኤጄንሲ ጉዳዩን እንደደረሰበት ለዋና ተቆጣጣሪ የመራ መሆኑንና ገዲብ አመራሮች በሥፍራው ተገኝንተው ያካሔዱትን ምርመራ ተከትሎ በደረሰበት የፕሮግራሞች ክለሳ መሠረት የምግብ እርዳታውን በጊዜያዊነት መግታት ተመራጭ ግብራዊ እርምጃው አድርጎ ለመሰድ እንደበቃ አመላክቷል።

ጉዳዩን አስመልክቶም፤ የዩናይትድ ስቴትስ መንግሥት ለኢትዮጵያ የፌዴራል መንግሥትና የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ባለ ስልጣናት ማቅረቡንና ኃላፊነቱ የሚመለከታቸውን ለይተው ተጠያቂ እንደሚያደርጉ የተነገረው መሆኑም ተነግሯል።

ኤጄንሲው የገታውን የምግብ እርዳታ ዳግም የሚጀምረው ጠንካራ የቁጥጥር እርምጃዎች ግብር ላይ ሲውሉ ብቻ እንደሆነ አፅንዖት ሰጥቶ አሳስቧል።

አቶ ጌታቸው ረዳ፤ የትግራይ ክልል ጊዘያዊ አስተዳደር ፕሬዚደንት በበኩላቸው በከፍተኛ ደረጃ" ምርምራ ማስጀመራቸውን ገልጠው፤ ዓለም አቀፉ የረድኤት ድርጅቶች በዘርፈ ብዙ ልገሳቸው እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅርበዋል።


1 min read

Published

By Stringer Report

Source: SBS


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now