የቡድን 7 ዋነኛ ዲፕሎማቶች በምጣኔ ሃብት ቀውስ ላይ አተኩረው በአገረ ጀርመን ታድመዋል

በቀድሞው የፓኪስታን ጠቅላይ ሚኒስትር ኢምራን ከሃን ላይ የግድያ ሙከራ በመቃጣት ተጠርጣሪ የተባለ አንድ ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ።

Diplomats.jpg

(L-R) High Representative of the EU for Foreign Affairs and Security Policy, Josep Borrell, British Secretary of State for Foreign Affairs James Cleverly, Japanese Foreign Minister Yoshimasa Hayashi, US Secretary of State Antony Blinken, German Foreign Minister Annalena Baerbock Canadian Foreign Minister Melanie Joly, French Foreign Minister Catherine Colonna, and Italian Foreign Minister Antonio Tajani pose for a family photo during of the G7 Foreign Ministers summit at the historical city hall on November 3, 2022 in Muenster, Germany Credit: Friedemann Vogel - Pool/Getty Images

የዓለም ዋነኛና ባለ ኢንዱስትሪ አገራት ቡድን 7 ገዲብ ዲፕሎማቶች ለሁለት ቀናት ውይይት በምዕራብ ጀርመን ሙኢንስተር ከተማ ታድመዋል።

የንግግራቸው ትኩረት በሩስያና ዩክሬይን ጦርነት ሳቢያ በተከሰቱት የምግብና የኃይል ምንጭ እጥረቶች፣ እንዲሁም ከአውሮፓ ርቆ ባሳደራቸው ተፅዕኖዎች ላይ ነው።

ታዳሚዎቹ የቡድን 7 አገራት እንግሊዝ፣ ካናዳ፣ ፈረንሳይ፣ ጀርመን፣ ጣሊያን፣ ጃፓንና ዩናይትድ ስቴትስ ናቸው።  


ኢምራን ከሃን

የቀድሞው የፓኪስታን ጠቅላይ ሚኒስትር ኢምራን ከሃን ላይ የመግደል ሙከራ በማድረግ ተጠርጣሪ የሆነ አንድ ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ።

ማንነቱ ይፋ ያልሆነው ተጠርጣሪ ግለሰብ የቀድሞውን ጠቅላይ ሚኒስትር ለመግደል እንደሞከረና ያንንም ያደረገው ያለ ማንም እገዛ ብቻውን እንደሆነ ተናግሯል።

እግራቸው ላይ የመቁሰል አደጋ የደረስባቸው የ70 ዓመቱ ከሃን በአሁኑ ወቅት በሻዩካት ከሃኑም ሆስፒታል የሚገኙ ሲሆን፤ ቀዶ ሕክምና የተደረገላቸውና በደኅና ሁኔታም የሚገኙ መሆኑን ዶ/ር ፋይዛል ሱልጣን ገልጠዋል።

ከሃን በጥይት የግድያ ሙከራ የደረሰባቸው የተቃውሞ ሰልፍ ተገኝተው ባሉበት ወቅት ነው።

 





 






 




Share

Published

By Kassahun Seboqa Negewo, NACA
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service