ሙዚቀኛ ዳዊት ፍሬው ኃይሉ በአረፈበት ሆቴል ሕይወቱ አልፎ ተገኘ

ሙዚቀኛው በኢትዮጵያ ኤምባሲ በጣሊያን ሮም ከተማ ሥራዎቹን አቅርቦ ወደ አረፈበት ሆቴል ከገባ በኋላ ምክንያቱ ለጊዜው ባልታወቀ ሁኔታ ማረፉን የጣሊያን ፖሊሶች መናገራቸው ተዘግቧል።

Artist Dawit Frew Hailu.jpg

Dawit Frew Hailu. Credit: PR

በመሳሪያ የተቀነባበሩ አልበችሞን በማሳተም እንዲሁም በርካታ መድረኮች ላይ የሙዚቃ መሳሪያ በመጫዎት ከፍተኛ አድናቆትን ያተረፈው የአንጋፋው ድምፃዊ ጋሽ ፍሬው ኃይሉ ልጅ ሙዚቀኛ ዳዊት ፍሬው ለሥራ በሄደበት ጣሊያን ሮም ትላንት ምሽት በአረፈበት ሆቴል ሕይወቱ ማለፉ ተነግሯል ።

ሙዚቀኛው በኢትዮጵያ ኤምባሲ በጣሊያን ሮም ከተማ ሥራዎቹን አቅርቦ ወደ አረፈበት ሆቴል ከገባ በኋላ ምክንያቱ ለጊዜው ባልታወቀ ሁኔታ ማረፉን የጣሊያን ፖሊሶች መናገራቸው ተዘግቧል።

በጣሊያን የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን እና የሙያ አጋሮቹ ከአገሪቱ ፖሊስ ጋር ተነጋግረው የአርቲስቱን አስክሬን በአገሩ ለማሳረፍ እንቅስቃሴ መጀመራቸውም ታውቋል::

ዳዊት ፍሬው የክላርኔት የሙዚቃ መሳሪያውን እየተጫወተ የሠራው ሶስት የሙዚቃ አልበም ያለው ሲሆን የአንጋፋው ድምፃዊ ፍሬው ሀይሉ ልጅም ነው።


1 min read

Published

By Stringer Report

Source: SBS


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now