SKIP TO MAIN CONTENT

ሙዚቀኛ ዳዊት ፍሬው ኃይሉ በአረፈበት ሆቴል ሕይወቱ አልፎ ተገኘ

ሙዚቀኛው በኢትዮጵያ ኤምባሲ በጣሊያን ሮም ከተማ ሥራዎቹን አቅርቦ ወደ አረፈበት ሆቴል ከገባ በኋላ ምክንያቱ ለጊዜው ባልታወቀ ሁኔታ ማረፉን የጣሊያን ፖሊሶች መናገራቸው ተዘግቧል።

Artist Dawit Frew Hailu.jpg
Dawit Frew Hailu. Credit: PR

1 min read

Published

By Stringer Report

Source: SBS


Skip to article content

በመሳሪያ የተቀነባበሩ አልበችሞን በማሳተም እንዲሁም በርካታ መድረኮች ላይ የሙዚቃ መሳሪያ በመጫዎት ከፍተኛ አድናቆትን ያተረፈው የአንጋፋው ድምፃዊ ጋሽ ፍሬው ኃይሉ ልጅ ሙዚቀኛ ዳዊት ፍሬው ለሥራ በሄደበት ጣሊያን ሮም ትላንት ምሽት በአረፈበት ሆቴል ሕይወቱ ማለፉ ተነግሯል ።

ሙዚቀኛው በኢትዮጵያ ኤምባሲ በጣሊያን ሮም ከተማ ሥራዎቹን አቅርቦ ወደ አረፈበት ሆቴል ከገባ በኋላ ምክንያቱ ለጊዜው ባልታወቀ ሁኔታ ማረፉን የጣሊያን ፖሊሶች መናገራቸው ተዘግቧል።

በጣሊያን የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን እና የሙያ አጋሮቹ ከአገሪቱ ፖሊስ ጋር ተነጋግረው የአርቲስቱን አስክሬን በአገሩ ለማሳረፍ እንቅስቃሴ መጀመራቸውም ታውቋል::

ዳዊት ፍሬው የክላርኔት የሙዚቃ መሳሪያውን እየተጫወተ የሠራው ሶስት የሙዚቃ አልበም ያለው ሲሆን የአንጋፋው ድምፃዊ ፍሬው ሀይሉ ልጅም ነው።


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Stream now