"የሰላም ንግግሩ ስምምነት የትግራይን ሕዝብ ፍላጎቶች ማዕከል በማድረግ የሚተገበር ይሆናል" የትግራይ የሕዝብ ግንኙነት ቢሮ

"የተጎዳችው ኢትዮጵያ ነበረች፣ የተጎዳነው ሁላችንም ነበርን፤ በሁላችንም ጥቅም የጋራ ኢትዮጵያችንን ከፍ የማድረግ ሃሳብ ነው ያለው" አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን

Redwan Hussein (2nd L), Representative of the Ethiopian government, and Getachew Reda (2nd R), Representative of the Tigray People's Liberation Front (TPLF).jpg

Redwan Hussein (2nd L), Representative of the Ethiopian government, and Getachew Reda (2nd R), Representative of the Tigray People's Liberation Front (TPLF), sign a peace agreement between the two parties during a press conference regarding the African Union-led negotiations to resolve conflict in Ethiopia at the Department of International Relations and Cooperation (DIRCO) offices in Pretoria on November 2, 2022. Credit: PHILL MAGAKOE/AFP via Getty Images

የትግራይ የሕዝብ ግንኙነት ቢሮ ትናንት ጥቅምት 25 ከመቀሌ ባወጣው መግለጫ የሰላም ንግግሩ ስምምነት የትግራይን ሕዝብ ፍላጎቶች ማዕከል በማድረግ የሚተገበር መሆኑን ገለጠ።

መግለጫው ሕወሓትን በስም ሳይጠቅስ "የትግራይ መንግሥት" በማለት የተጠቀመ ሲሆን፤ "ውድመትን በመግታት ለሕዝባችን ምቹ ሰላማዊ ሕይወትን ለመፍጠር ሕዝብና የትግራይ መንግሥት ተደጋጋሚ ጥሪዎችን ማቅረባቸው የሚታወቅ ነው" ብሏል።

በማከልም፤ የደቡብ አፍሪካውን የሰላም ንግግር ከግጭት መገታት ስምምነት ጠቅሶ ሁነኛ ያላቸውን ግቦች ሲያመላክት " የወራሪዎች ከትግራይ መውጣትና ገደብ አልባ ሰብዓዊ ረድኤቶች ወደ ትግራይ እንዲዘልቁ" መሆኑን ጠቅሷል።

ቢሮው የስምምነቱ ዋነኛ ስኬት "የሕገ መንግሥትና ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓት ከበሬታ" እንደሆነም አመላክቷል።

አክሎም፤ የስምምነቱን ዝርዝር በተመለከተ 'የትግራይ መንግሥት' ማብራሪያዎችን በተከታታይ እንደሚሰጥ ጠቁሞ፤ የትግራይን ሕዝብ ሕልውና የሚጎዳ ስምምነትንም ሆነ ተግባርን እንደማይቀበልም አስታውቋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለም፤ በአፍሪካ ኅብረት ሸምጋይነት በተመራው የደቡብ አፍሪካ የሰላም ንግግር ላይ የኢትዮጵያ መንግሥት ልዑክ ቡድን መሪ ሆነው በመገኘት ስምምነቱ ላይ ፊርማቸውን ያኖሩት የሰላም አማራጭ ዐቢይ ኮሚቴ አባልና የጠቅላይ ሚኒስትሩ የብሔራዊ ደኅንነት አማካሪ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን በበኩላቸው ትናንት ጥቅምት 25 ለከፍተኛ የመንግሥት አመራር አባላት ገለጣ አድርገዋል።

በአምባሳደሩ የሰላም ስምምነት ገለጣ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድን አክሎ የሁለቱ ምክር ቤቶች አፈ ጉባኤዎች፣ የክልል ርዕሰ መስተዳድሮች፣ ከፍተኛ የመንግሥት አመራሮችና የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላዎች ተገኝተዋል።

አምባሳደር ሬድዋን የገለጣቸውን ዋነኛ ጭብጮች አስመልክተው ለአገር ውስጥ ብዙኅን መገናኛ ባስረዱበት ወቅት፤ የሕገ መንግሥታዊ ሥርዓት መከበርን ማረጋገጥና ሉዓላዊነትን በማስከበር በኩል ከመተማመን ላይ እንደተደረሰ፣ የሽግግር ጊዜ ሂደትን፣ የወደሙትን መጠገንን፣ የደረሱ ጥፋቶችን መልሶ መመልከትን፣ አንድነትንና በጋራ ተያይዞ መቀጠልን ያቀፈ ስለመሆኑ በአንኳርነት አንስተዋል።

Share

Published

Updated

By Kassahun Seboqa Negewo
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service