"የይሁዳ ክህደት" የነባር ዜጎች መሪ ኖል ፒርሰን የሊብራል ፓርቲን በክህደት ፈረጁ

ጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልባኒዚ የሙስሊሙ ማኅበረሰብ በአንድነት ቆሞ ድጋፉን ለድምፅ ለፓርላማ እንዲቸር ጥሪ አቀረቡ።

Noel Pearson .jpg

Noel Pearson at Sydney Town Hall on November 5, 2014, in Sydney, Australia. Credit: Peter Rae - Pool/Getty Images

የአውስትራሊያ ነባር ዜጎች መሪ ኖል ፒርሰን የሊብራል ፓርቲ ለነባር ዜጎች ድምፅ ለፓርላማ እንዳይመሠረት የአውስትራሊያ ሕዝብ ላይ በፋሲካ ዋዜዋ "የይሁዳን ክሕደት" ፈፅሟል ሲሉ የከረረ ትችት ሰነዘሩ።

አቶ ፒርሰን የነባር ዜጎች ድምፅ ለፓርላማ እንዲመሠረትና በሕገ መንግስቱም ውስጥ እንዲሠፍር ጥሪ ያቀረበው የኡሉሩ መግለጫ አርቃቂና አውጪ ከሆኑት መሪዎች አንዱ ናቸው።

 እንዲህ ላለው ብርቱና በእጅጉ ጠቃሚ አገራዊ ጉዳይ ድጋፍን መንሳት በእጅጉ አሳዛኝ እንደሆነ አመላካተው፤ የተቃዋሚ ቡድን መሪ ፒተር ዳተን ድምፅ ለፓርላማን ተፃርሮ መቆም "አገሪቱን ሃፍረት ያላብሳል" ሲሉ ለSBS ተናግረዋል።

አክለውም "እሱ [ፒተር ዳተን] ኡሉሩን ለመቅብር ይሞክራል፤ ይሁንና ይሳካላታል ብዬ አላስብም። የዳተንና ፖሊን ሃንሰን የጋራ ቲኬት ለስኬት ይበቃል ብዬ አላስብም። በምንም ዓይነት ለስኬት መብቃት የለበትም። አገሪቱ ለወደፊት ዕጣ ፈንታዋ ከዚህ የተሻለ ይገባታል" ብለዋል።

በሌላም በኩል፤ የቀድሞው የሊብራል ፓርቲ ነባር ዜጎች ሚኒስትር የነበሩት ኬን ዋይት በአቶ ዳተን ድምፅ ለፓርላማ ተፃራሪ አቋም ሳቢያ የሊብራል ፓርቲ አባልነታቸውን ሰርዘዋል።

አቶ ዳተን ድምፅ ለፓርላማን ተቃውመው የሕገ መንግሥት ሕዝበ ውሳኔ ዘመቻ እንደሚያካሂዱና ሆኖም ምልክታዊ የሆነ ሕገ መንግሥታዊ ዕውቅና ቢያገኙ የማይቃወሙ መሆናቸው ትናንት ይፋ አድረገዋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለም፤ ጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልባኒዚ የሙስሊሙ ማኅበረሰብ በአንድነት ቆሞ ድጋፉን ለድምፅ ለፓርላማ እንዲቸር ጥሪ አቅርበዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ የድምፅ ለፓርላማ ጥሪያቸውን ያቀረቡት የአውስትራሊያ ሙስሊም ወዳጅነት ባዘጋጀው ብሔራዊ ኢፍጣር የእራት ግብዣ ላይ ተገኝተው ነው።

 የአቦርጂናልና ቶረስ መሽመጥ ደሴተኞች ሕገ መንግሥታዊ ዕውቅናን ማላበስ ለአውስትራሊያ ሕብረትና አንድነትን ማጎናፀፊያ ወቅት እንደሆነ አስገንዝበዋል።



 

Share

Published

Updated

By Kassahun Seboqa Negewo, NACA
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service