የኑሮ ውድነትን መቋቋም ያቃታቸው ጋናውያን ፕሬዚደንት ናና ከስልጣን እንዲለቁ ጠየቁ

አውስትራሊያ በ2026 የተባበሩት መንግሥታት የአየር ንብረት ለውጥ ኮንፈረንስ COP31 አስተናጋጅ አገር ለመሆን ፈቃደኝነቷን ገለጠች።

President of Ghana Nana Akufo-Addo.jpg

President of Ghana Nana Akufo-Addo (L), and Ghanaians march during the ‘Ku Me Preko’ demonstration on November 5, 2022, in Accra, Ghana (R). Credit: Paul Marotta/Getty Images / Ernest Ankomah/Getty Images

በጋና መዲና አክራ በሺህዎች የሚቆጠሩ ተቃዋሚ ሰልፈኞች ፕሬዚደንት ናና አኩፎ አዶ ከስልጣን እንዲለቁ ጠየቁ።

በቁጣ የተመሉት የተቃውሞ ሰልፈኞች ፕሬዚደንቱ ከስልጣን እንዲለቅቁ ድምፃቸውን ያሰሙት ለጋና ከሬኮር ያለፈ የነዳጅና ምግብ ዋጋ ማሻቀብ ተጠያቂው ፕሬዚደንቱ ናቸው በሚል ዕሳቤ ነው።
 
ቀይ ካናቴራ ያጠለቁት ተቃዋሚ ሰልፈኞች አክራ አደባባይ ላይ ይዘዋቸው ከወጡት መፈክሮች ውስጥ "አኩፎ አዶ የግድ መሰናበት አለባቸው" እና የጋናውን ፕሬዚደንት ከዓለም የገንዘብ ድርጅት ጋር እያካሔዱ ያለውን ድርድር በማመላከትም "እምቢኝ ለዓለም ገንዘብ ድርጅት" የሚሉ መፈክሮች ይገኙባቸዋል።

የጋና ገንዘብ ከሌሎች የምዕራብ አፍሪካ አገራት ጋር ሲነፃፀር ምንዛሪው በ40 ፐርሰንት ያሽቆለቆለ ነው።
 
በዓለም ባንክ መረጃ መሠረት ሩብ ያህል ጋናውያን የሚኖሩት በቀን 2.15 የአሜሪካ ዶላር ባነሰ ገቢ ነው።

የአየር ንብረት ለውጥ

አውስትራሊያ የተባበሩት መንግሥታትን የአየር ንብረት ለውጥ ኮንፈረንስ በ2026 ለማዘጋጀት ፈቃደኛ መሆኗን አስታወቀች።

የአውስትራሊያን የ2026 የተመድ አየር ንብረት ለውጥ ኮንፈረንስ የማስተናገድ ፈቃደኝነት ዛሬ ማለዳ ላይ የገለጡት የአየር ንብረት ለውጥ ሚኒስትር ክሪስ ባወን ናቸው።

ሚኒስትሩ የአውስትራሊያ መንግሥት ካቢኔ በ2026 አውስትራሊያ የCOP31 አስተናጋጅ አገር ለመሆን ፈቃዱ መሆኑን በስምምነት ያረጋገጠላቸው መሆኑንም ጠቅሰዋል።

የ2024 የተመድ የአየር ንብረት ለውጥ ኮንፈረንስ ለምሥራቅ አውሮ ፓ አገር የተሰጠ ሲሆን የ2026 ኮንፈረንስ ለምዕራብ አውሮፓና ሌሎች ፈቃደኛ አገራት በታሳቢነት የተያዘ ነው።



Share

Published

By Kassahun Seboqa Negewo, NACA
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service
የኑሮ ውድነትን መቋቋም ያቃታቸው ጋናውያን ፕሬዚደንት ናና ከስልጣን እንዲለቁ ጠየቁ | SBS Amharic