ሞሮኮና ስፔይን ዛሬ ማለዳ በኳታር የትምህርት ከተማ ስታዲየም ባካሔዱት የጥሎ ማለፍ ግጥሚያ ሞሮኮ 3 ለ 0 በሆነ ውጤት ለቀጣዩ የዓለም ዋንጫ ሩብ ፍፃሜ ለማለፍ በቅታለች።
ሞሮኮ ሶስቱን ግቦች ያስቆጠረችው በሙሉና ተጨማሪ 120 ደቂቃዎች ያለ ግብ አቻ በመውጣታቸው በመለያ ፍጹም ቅጣት ምት ነው።
የ2010 የዓለም ዋንጫ ባለቤት የነበረችውን ስፔይንን ድል የነሳችው ሞሮኮ በዓለም ዋንጫ ውድድር ታሪኳ ለሩብ ፍፃሜ ስትበቃ ይህ የመጀመሪያ ጊዜዋ ነው።
ከስፔይን የመለያ ፍፁም ቅጣት ምት መቺዎችን ሰርጂዮ ባስኩዌትስ፣ ካርሎስ ሶሌር እና ፓብሎ ሳራብያ የተመቱ ኳሶችን መረብ ላይ እንዳያርፉ በመያዝ ቡድኑን ለድል ያበቃው ግብ ጠባቂ ያሲን ቦዩኑ የሞሮኮ አንፀባራቂ ኮከብ ለመሆን በቅቷል።

Yassine Bounou goal keeper of Morocco blocks his third penalty kick during the FIFA World Cup Qatar 2022 Round of 16 match between Morocco and Spain at Education City Stadium on December 06, 2022 in Al Rayyan, Qatar. Credit: Lionel Hahn/Getty Images

Rafael Leao of Portugal celebrates after scoring a goal to make it 6-1 during the FIFA World Cup Qatar 2022 Round of 16 match between Portugal and Switzerland at Lusail Stadium on December 6, 2022 in Lusail City, Qatar. Credit: Matthew Ashton - AMA/Getty Images
የሩብ ፍፃሜ ግጥሚያ ሠንጠረዥ
ብራዚል እና ክሮኤሽያ (ቅዳሜ ዲሴምበር 10 / ታሕሳስ 1) 2:00 am [AEDT]
ኔዘርላንድስ እና አርጀንቲና (ቅዳሜ ዲሴምበር 10 / ታሕሳስ 1) 6:00 am [AEDT]
ሞሮኮ እና ፖርቹጋል (እሑድ ዲሴምበር 11 / ታሕሳስ 2) 2:00 am [AEDT]
እንግሊዝ እና ፈረንሳይ (እሑድ ዲሴምበር 11 / ታሕሳስ 2) 6:00 am [AEDT]