ጆ ባይደን በአብላጫ ድምፅ እንደሚያሸንፉ ያላቸውን እምነት ገለጡ

*** ቪክቶሪያ ላይ ተጥለው ያሉ የኮሮናቫይረስ ገደቦች መላላት ነገ ይፋ ይሆናል

US Election 2020

Joe Biden has delivered a speech from Delaware, urging unity among the American people. Source: AFP

የዲሞክራቱ ዕጩ ፕሬዚደንት ጆ ባይደን በፕሬዚደንት ትራምፕ ላይ ያላቸው አብላጫ ድምፅ እየጨመረ መምጣትን ተከትለው 46ኛው የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚደንት እንደሚሆኑ ያላቸን ሙሉ ተስፋ ገልጠዋል።

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚደንት ለመሆን 270 የምርጫ ኮሌጅ ድምፆችን ማሸነፍ ግድ ይላል። አቶ ባይደን በአሁኑ ወቅት በፎክስ ኒውስ ስሌት 264 የምርጫ ድምፆችን ያሸነፉ ሲሆን በCNN ስሌት 253 ድምፆችን አግኝተዋል።

ይሁንና ከሚያሻቸው የምርጫ ኮሌጅ ድምፆች በላይ የሚያስገኙላቸውን ፔንሲልቫኒያ (20)፣ አሪዞና (11)፣ ጂርጂያ (16) እና ኔቫዳ (6) እየመሩ ይገኛሉ። አቶ ባይደን የፔንሲልቫኒያን 20 የምርጫ ኮሌጅ ድምፅ ብቻ ካሸነፉ ቀጣዩ የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚደንት ለመሆን ከሚያሻቸው 270 ድምፆች በላይ የሚያስገኝላቸው ሲሆን በእሳቸው ግምት ከ300 በላይ የምርጫ ኮሌጅ ድምፆችን እንደሚያሸንፉ ያላቸውን እምነት ገልጠዋል።

ከጠቅላላ የመራጮች ድምፅ ውስጥም አቶ ባይደን እስካሁን ከ74 ሚሊየን በላይ ሲያሸንፉ አቶ ትራምፕ ከ70 ሚሊየን በላይ በላይ ድምፆችን በማግኘት እየተከተሉ ይገኛሉ። 

አቶ ትራምፕ ግና ምንም እንኳ ይህ ነው የሚባል ማስረጃ ባያቀርቡም በምርጫ ሂደቱ የተጭበረበሩ ድምፆች አሉ በማለት ቁልፍ በሆኑ ስቴቶች የድምፅ ቆጠራው እንዲቆም ወይም ዳግም ቆጠራ እንዲደረግ ወደ ጠቅላይ ፍርድ ቤት እንደሚያመሩ አስታውቀዋል።  

ይህንንም በተመለከተ ጠቅላይ ሚኒስትር ስኮት ሞሪሰን ማንም ይመረጥ ማን ቀደም ሲል ከነበሩት ፕሬዚደንት ጋር አብረው እንደሠሩ ሁሉ ከቀጣዩ የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚደንት ጋርም በጋራ እንደሚሰሩ ገልጠዋል።

  ቫይረስ ቪክቶሪያ

 

 ቪክቶሪያ እስከ ዛሬ ቅዳሜ ኖቬበር 7 ላለፉት ስምንት ቀናት በኮረናቫይረስ የተያዘም ሆነ ሕይወቱ ያለፈ ግለሰብ ሳታስመዘግብ ቆይታለች። 

በነገው ዕለት እሑድ ኖቬበር 8 እስካሁን ተጥለው ያሉት የኮሮናቫይረስ ገደቦችን መርገብ አስመክቶ ፕሪሚየር ዳንኤል አንድሩስ መግለጫ ይሰጣሉ።

የቪክቶሪያ ጤና ሚኒስትር ማርቲን ፎሊ ቪክቶሪያ እየካሄደች ያለችው የወረርሽኝ መከላከል ዘለቄታ እንዲኖረው ማስቀጠል ግድ እንደሚሆን አሳስበዋል። 

 

 

 

 

 

 

 

 


Share

Published

By NACA
Presented by Kassahun Seboqa Negewo

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service