የእሥራኤልና እስላማዊ ጂሃድ የጋዛ ተኩስ አቁም ስምምነት ግብር ላይ ዋለ

ለአረጋውያን ክብካቤ ሠራተኞች የደመወዝ ጭማሪ ሊደረግ ነው

Gaza.jpg

A man reacts after a coach was hit by an Israeli airstrike leaving three people dead in Gaza on 7 August, 2022. Source: Getty / Anadolu Agency via Getty Images

በግብፅ አደራዳሪነት ከእስላማዊ ጂሃድ ጋር የጋዛ ተኩስ አቁም ግብር ላይ መዋሉን እሥራኤል አስታወቀች።

በእስራሌልና ጋዛ በሚገኘው እስላማዊ ጂሃድ መካከል ለሶስት ተከታታይ ቀናት በተካሔደ ግጭት የሮኬት ውንጨፋና የአየር ድብደባዎች ተካሂደዋል።

በግጭቱ ሳቢያም 15 ሕፃናትን ጨምሮ 43 ያህል ሰዎች ተግድለዋል፤ በመቶዎች የሚቆጠሩ የመቁሰል አደጋ ደርሶባቸዋል።
 
የእስላማዊ ጂሃድ ባለስልጣን ዳውድ ሺሃብ በግብፅ አማካይነት የሼክ ባሳም አል ሳዲ እና ክሃሊ አዋዴህን ከእሥር የማስለቀቅ ቃል ተከትሎ በፍልስጤም በኩል ድርጅታቸው የተኩስ አቁም ስምምነቱን እንደሚያከብር ገልጠዋል።

***

የአውስትራሊያ የሥራ ፍትሕ ኮሚሽን ለአረጋውያን ክብካቤ ሠራተኞች የደመወዝ ጭማሪ ለማድረግ አስቧል።

 ለሠራተኞቹ ምን ያህል የደመወዝ ጭማሪ እንደሚደረግ ለኮሚሽኑ በሚቀርበው ምክረ ሃሳብ አዘል ደብዳቤ ላይ እንደሚገለጥ ተጠቁሟል።

የሌበር ሚኒስትር ታንያ ፒልበርስክ መንግሥት ለደመወዝ ጭማሪው የገንዘብ ድጎማ እንደሚያደርግና በሰዓት $22 ክፍያ ከሠራተኞቹ አገልግሎት ጋር ተመጣጣኝ እንዳልሆነ ተናግረዋል።

 



 



 







Share

Published

By NACA, Kassahun Seboqa Negewo
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service