ዩናይትድ ስቴትስ ውስጥ የስድስት ዓመት ልጅ መምህርቱን ተኩሶ አቆሰለ

ሜዲቲራኒያን ባሕር ላይ 16 ወላጅ / ሞግዚት አልባ ልጆችን ጨምሮ ከ70 በላይ ፍልሰተኞች በድንገተኛ አደጋ ደራሽ ሠራተኞች ለትድግና በቁ

A teacher was injured in a shooting Friday afternoon.jpg

A teacher was injured in a shooting Friday afternoon, Jan. 6, 2023, at Richneck Elementary School in Newport News, Virginia, according to police and school officials. Credit: Billy Schuerman/The Virginian-Pilot/Tribune News Service via Getty Images)

አንድ የስድስት ዓመት ተማሪ ዓርብ ዕለት መምህርቱን መማሪያ ክፍል ውስጥ ተኩሶ ማቁሰሉን የኒው ፖርት ኒውስ ክተማ ፖሊስና የትምህርት ቤቱ ኃላፊዎች አስታወቁ።

ምንም እንኳ የስድስድት ዓመት ልጅ ሰውን ተኩሶ የማቁሰል ድርጊት ከዚህ ቀደም እንግዳ ባይሆንም እጅግም የተለመደ አለመሆኑን የመስኩ ተጠባቢዎች አመላክተዋል።

በፖሊስ ገለጣ መሠረት አደጋው ከደረሰበት የሪችኔክ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አንድም የቆሰለ ተማሪ የለም።

በስድስት ዓመቱ ተማሪ የቆሰለችውና በ30ዎቹ ዕድሜ ውስጥ ያለችው መምህርት የደረሰባት የመቁሰል አደጋ ብርቱ ሲሆን ከቀትር በኋላ ግና መጠነኛ መሻሻል ማሳየቱም ተነግሯል።

የስድስት ዓመቱ ልጅ በፖሊስ ቁጥጥር ስር እንደሚገኝ የኒው ፖርት ኒውስ ፖሊስ አዛዥ ስቲቭ ድሩ አስታውቀዋል።

ፍልሰተኞች

ከሊቢያ ወደ አውሮፓ በሜዲቲራኒያን ባሕር አቋርጠው ለማለፍ ሲሞክሩ የነበሩ 73 ፍልሰተኞች በድንገተኛ አደጋ ደራሽ ሠራተኞች ለትድግና በቅተዋል።

16 ወላጅ / ሞግዚ አልባ ልጆችን አክሎ 73ቱን ፍልሰተኞቹን እንደታደጉት ድንበር አልባ ሐኪሞች ምግባረ ሰናይ ድርጅት ገለጣ፤ ግለሰቦቹ ይጓዙ የነበሩት ሚዛኗን ባልጠበቀችና ከመጠን በላይ በጫነች የጎማ ጀልባ ነበር።

ግለሰቦቹ ከጀልባይቱ ወደ ድንገተኛ አደጋ ደራሽ ሠራተኞች መርከብ የተዘዋወሩ ሲሆን፤ የሕክምና ምርመራ ከተደረገላቸው በኋላ ወደ አንድ የተመረጠ ወደብ ተጓጉዘው እንዲወረዱ የሚደረግ ይህናል።


 
 







Share

Published

Updated

By Kassahun Seboqa Negewo, NACA
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service