የሃማስ ታጣቂዎች የእሥራኤልን ሲቪልና ወታደሮች በቁጥጥር ስር ማዋልና መግደል በኋላ የእሥራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ እሥራኤል ጦርነት ላይ እንደሆነችና በአፀፋውም 'ግዙፍ የበቀል እርምጃ' እንደሚወስዱ አስታወቁ።
ቃላቸውን ተከሎም እሥራኤል በጋዛ ሰርጥ ብርቱ የአየር ጥቃት ፈፅማለች።
ቢያንስ 250 ያህል እሥራኤላውያን ሕይወታቸውን ሲያጡ ከ1100 በላይ ከ20 በበለጡ የእሥራኤል ክፍለ ከተሞች የቀላል መሣሪያዎች ተኩስ ልውውጥ ቆስለዋል።

በፍልስጤማውያን በኩል ከ232 በላይ ሕይወታቸው ሲያጡ 1600 ቆስለዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ኔታንያሁ "ለጥቁሩ ቀን ግዙፍ የበቀል እርምጃ እንወስዳለን"
"የምንገኘው ጦርነት ላይ ነው፤ እናሸንፋለንም" ሲሉ፤
የሃማስ መሪ ኢስማኢሊ ሃኒየህ በበኩላቸው ጋዛ ላይ የተጀመረው ወደ ምዕራብ ባንክና ኢየሩሳሌም እንደሚቀጥል ተናግረዋል።

የአውስትራሊያ ጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልባኒዚንና የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚደንት ጨምሮ በርካታ እሪዎች ከእሥራኤል ጎን እንደሚቆሙ አስታውቀዋል።

