የጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልባኒዚ የሕንድ ጉዞ የሰብዓዊ መብቶች ጥያቄ አጥልቶበታል

የሰሜን አትላንቲክ ጦር ቃልኪዳን ድርጅት፤ ሩስያ የምሥራቃዊ ዩክሬይን ከተማ ባክህሙትን በቅርቡ ልትቆጣጠር እንደምትችል አመለከተ።

PM Narendra Modi and Prime Minister Anthony Albanese.jpg

Questions about Narendra Modi's role in the Gujarat riots have resurfaced as Prime Minister Anthony Albanese travels to India. Credit: SBS News

ጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልባኒዚ ከአውስትራሊያ የንግድ ልዑካንና የዩኒቨርሲቲ መሪዎች ጋር ሆነው ሕንድ ገቡ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሕንድ እንደደረሱ በሕንዱ አቻቸው ናሬንድራ ሞዲ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።

አቶ አልባኒዚ በጉጃራት ተገኝተው ሳባርማቲ አሽራምና የነፃነት ተፋላሚውን ማሃታማ ጋንዲን መታሰቢያ ጎብኝተዋል።

 የአውስትራሊያ ልዑካን ቡድን ለሶስት ቀናት በሕንድ አህመዳባድ ከተማ የሚቆዩ ሲሆን፤ ትኩረታቸው የሁለትዮሽ ግንኙነቶችን ማጠናከር ላይ ይሆናል።

ይህ በእንዲህ እንዳለም፤ የጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልባኒዚን የሕንድ ጉዞ ተከትሎ በተለይም በሕንድ ሙስሊሞች ላይ የደረሱት የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች ትኩረት የሚያገኙ ይሆናሉ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ስልጣን ከጨበጡ ወዲህ የሂንዱ ብሔረተኛነት የከረረ መሆኑን የሰብዓዊ መብቶች ድርጅቶችና የፖለቲካ ተጠባቢዎች እያመላከቱ ነው።
Religion in India.jpg
Credit: Indian census, 2011
ዩክሬይን

የሰሜን አትላንቲክ ጦር ቃልኪዳን ድርጅት ዋና ፀሐፊ የንስ ስቶልቴንበርግ ሩስያ የምሥራቃዊ ዩክሬይን ከተማ ባክህሙትን በቅርቡ ልትቆጣጠር እንደምትችል ተናገሩ።

ዋና ፀሐፊው ትንበያቸውን የሰነዘሩት የአውሮፓ መከላከያ ሚኒስትሮች ስዊድንና ፊንላንድን ለድርጅቱ ለማስተዋወቅ በታደሙበት ስብሰባ ላይ ነው።

አቶ ስቶልቴንበርግ በዩክሬይን በኩል የሚቻለውን ያህል የመቋቋም ጥረት ቢደረግም ሩስያውያኑ ከተማይቱን ለመቆጣጠር ብርቱ እመርታ እያደረጉ መሆኑን በአፅንዖት ገልጠዋል።

 





Share

Published

By NACA, Kassahun Seboqa Negewo
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service