ሌበር ፓርቲ እስከ 40 ፐርሰንት የቤት ግዢ ድጎማ እንደሚያደርግ ገለጠ፤ የፌዴራል መንግሥቱ የኦንላይን ደኅንነት ጥበቃ ወጪ መደበ

*** የግብፅ የተፈጥሮ ጋዝ ማስተላለፊያ ቧንቧ ላይ ፍንዳታ ደረሰ

News

Leader of the Opposition Anthony Albanese (L) and Prime Minister Scott Morrison (R). Source: Getty

የሌበር ፓርቲ ከ10,000 በላይ ለሚሆኑ ቤት ገዢ አውስትራሊያውያን እስከ 40 ፐርሰንት የሚደርስ ድጋፍ እንደሚያደርግ አስታወቀ።

የቤት ግዢ ድጎማው ለአዲስ ቤት ገዢዎች እስክ 40 ፐርሰንት ተገንብተው ለቆዩ ቤት ገዢዎች እስከ 30 ፐርሰንት ይሆናል።

ድጎማው ለአዲስ ቤት ገዢዎች እስከ $380,000 ተገንብተው ለቆዩ ቤቶች ገዢዎች $285,000 ያህል የሚያስገኝ ሲሆን፤ እንደ የክፍለ አገራቱ ከ$550,000 እስከ  $950,000 የግዢ ጣራ ገደብ ተጥሎበታል። 

አውስትራሊያውያን ከፌዴራል መንግሥቱ ቤታቸውን መግዛት የሚችሉ ሲሆን ለግዢ ለመብቃት የሁለት ፐርሰንት ቀብድ መክፈልና የመደበኛ ብድር መስፈርቶችን ማሟላት ይጠበቅባቸዋል።  

የኦንላይን ደኅንነት ጥበቃ

ጠቅላይ ሚኒስትር ስኮት ሞሪሰን መንግሥታቸው ዳግም ከተመረጠ  ልጆች፣ ሴቶችን፣ ቤተሰቦችንና ትምህርት ቤቶችን ያካተተ የኦንላይን ደኅንነት ጥበቃ ወጪን እንደሚሸፍን አስታወቁ። 

በዚህም መሠረት $23 ሚሊየን የኢሴፍቲ ኮሚሽን በመላ አውስትራሊያ ላሉ መምህራን የስልጠና ፕሮግራሞችን እንዲያካሂድና የኦንላይን ደኅንነት ጥበቃ ማሻሻያ ይውላል።  

እንዲሁም የኢሴፍቲ ኮሚሽን ከሕግ አስከባሪ ኤጄንሲዎች ጋር ትብብር በማካሔድ ግልጋሎቶችን መስጠት እንዲችል $10 ሚሊየን እንዲሁም፤ ለመድብለ ባሕል ማኅበረሰባት የኦንላይን ደኅንነት ጥበቃ ግልጋሎት ማጠናከሪያ $2 ሚሊየን ተመድቧል።  

ሜይ 8 በጠቅላይ ሚኒስትር ስኮት ሞሪሰንና የሌበር መሪ አንቶኒ አልባኒዚ መከክል በ9 ኔትዎርክ አጋፋሪነት ለሁለተኛ ጊዜ የምርጫ ክርክር ይደረጋል። 

ግብፅ

በሰሜናዊ ሳይናይ ሰርጥ ባለ የተፈጥሮ ጋዝ ማስተላለፊያ ቧንቧ ላይ ፍንዳታ መድረሱን የግብፅ ባለስልጣናት አስታወቁ።

የቢር አል አብድ ከተማ የተፈጥሮ ጋዝ ማስተላለፊያ ቧንቧ ለፍንዳታ የዳረጉት ፈንጂዎቹ የተጠመዱት በሚሊሺያዎች መሆኑም ተገልጧል።

በፍንዳታው ወቅት ግዙፍ የእሳት ነበልባል አየር ላይ መጓኑንና ሆኖም በሰው ሕይወት ላይ ጥፋትም ሆነ ጉዳት አለመድረሱን ባለ ስልጣናቱ ተናግረዋል። 

እስካሁን ለፍናዳታው ኃላፊነቱን የወሰደ የለም።

 

 

 

 

 

              

 


Share

Published

Updated

By NACA
Presented by Kassahun Seboqa Negewo

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service