SKIP TO MAIN CONTENT

የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ አራተኛ ሙሌት መጠናቀቁ ተገለጠ

ለሁለት ቀናት የተካሔደው የኒው ዴልሂ 18ኛው የቡድን 20 አገራት የምጣኔ ሃብት ጉባኤ ዛሬ ተጠናቀቀ

GERD 4th round feeling.jpg
The fourth feeling of the Grand Ethiopian Renaissance Dam (GERD). Credit: PMOE

2 min read

Published

Updated

By Kassahun Seboqa Negewo, NACA

Source: SBS


Skip to article content

የኢትዮጵያ ታላቁ ሕዳሴ ግድብ አራተኛና የመጨረሻ ሙሌት ዛሬ እሑድ ጳጉሜን 5 መጠናቀቁን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አስታወቁ።

ለኢትዮጵያውያን ብሥራተ ዜናቸውን "በእንኳን ደስ አላችሁ" የገለጡት ጠቅላይ ሚኒስትር የአራቱን ዙር የግድብ ሙሌት ሂደት በምልሰት አንስተው "ብዙ ፈተና ነበረው፤ ወደኋላ እንድንመለስ ብዙ ተጎትተን ነበር። በውስጥ ፈተና በውጭ ጫና ነበረብን። ከፈጣሪ ጋር የመጣውን ሁሉ ተቋቁመን ለዚህ ደርሰናል።" ብለዋል።

አክለውም "ለግድቡ የምናደርገውን ማናቸውንም ድጋፍ እስከ ፍጻሜው እንድንቀጥል በዚሁ አጋጣሚ አደራ እላለሁ" ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል።

ቡድን 20

በኒው ዴልሂ ለ18ኛ ጊዜ ከጳጉሜን 4 እስከ 5 የተካሔደው የቡድን 20 አገራት የምጣኔ ሃብት ትብብር ጉባኤ ዛሬ ተጠናቅቋል።

ጉባኤውን በሊቀመንበርነት የመሩት የሕንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ናቸው።

አስተናጋጇና የጉባኤው ሰብሳቢ አገር ሕንድ የአረንጓዴ ልማት፣ የአየር ንብረት ለውጥ ፋይናንስና ሕይወት፣ ቴክኖሎጂያዊ ሽግግርና የዲጂታል ሕዝባዊ መሠረተ ልማት፣ የ21ኛ ክፍለ ዘመን ዘርፈ ብዙ ተቋማትና ሴቶች- መር ልማትን አክሎ ስድስት ዋነኛ የመወያያ አጀንዳዎች ለውይይት አቅርባለች።

በጉባኤው ሂደት ወቅት የአፍሪካ ሕብረት ሙሉ የቡድን 20 አባል መሆኑ ይፋ ተደርጓል።

ጉባኤው ባወጣው የጋራ ማጠቃለያ መግለጫው የዩክሬይንና ሩስያን ጦርነት አስመልክቶ ጦርነቱ "በእጅጉ ብርቱ ሰብዓዊ ሰቆቃን" አስከትሏል "ሁሉም መንግሥታት ከስጋት ፈጣሪነተንዲቆጠቡ" እና "ዘመኑ የጦርነት ዘመን ሊሆን አይገባም" ሲል ሩስያን ነጥሎ ከማውገዝ ተቆጥቧል።

ሆኖም፤ የአውስትራሊያ ጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልባኒዚ የቡድን 20 የጋራ መግለጫ የዩክሬይንን ጦርነት በማውገዝ ጠንካራ መልዕክት አስተላልፏል በማለት ተናግረዋል።

የሁለቱን ቀናት ጉባኤ ለማካሔድ ሕንድ 120 ሚሊየን የአሜሪካን ዶላር ወጪ አድርጋለች።

ሕንድ ለቀጣዩ የቡድን 20 አስተናጋጅ አገር ብራዚል የሰብሳቢነት ኃላፊነት አስረክባለች።


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Stream now