የዓለም ምግብ ድርጅት አስቸኳይ የገንዘብ እርዳታ ካላገኘ 750,000 ኢትዮጵያ ያሉ ስደተኞች 'የሚበሉት አይኖራቸውም' ሲል አሳሰበ

ከተመድ የተገኘ የ10 ሚሊየን ዶላር ብድር ለትግራይ ገበሬዎች ማዳበሪያ መርጃ እንደሚውል ተገለጠ

A girl cooks bread in a compound of abandoned buildings

A girls cooks bread in a compound of abandoned buildings, where internally displaced people are sheltered, near the town of Dubti, 10 kilometers from Semera, Ethiopia, on June 7, 2022። Credit: EDUARDO SOTERAS/AFP via Getty Images

የተባበሩት መንግሥታት ኤጄንሲዎችና የመንግሥት አገልግሎት ሰጪ ድርጅት ኢትዮጵያ ውስጥ ላሉ ከ750 ሺህ በላይ ስደተኞች ቀለብ ለመስፈር ለ73 ሚሊየን ዶላር አስቸኳይ እርዳታ አቤት አሉ።

አስቸኳይ እርዳታ ጠያቂዎቹ የዓለም ምግብ ፕሮግራም፣ የተመድ ከፍተኛ የስደተኞች ኮሚሽንና የኢትዮጵያ መንግሥት የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት ናቸው።

በምግባረ ሰናይ ድርጅቶቹ ማሳሰቢያ መሠረት የዓለም ምግብ ድርጅት ኦክቶበር ላይ ለስደተኞች የሚያቀርበው ምግብ አይኖረውም።

ለኢትዮጵያ የዓለም ምግብ ፕሮግራም ተወካይና ዳይሬክተር ክላውድ ጂቢዳር "አስቸኳይ የገንዘብ ድጎማ ካላገኘን የአንድ ሚሊየን ሶስት አራተኛ ስደተኞች በሳምንታት ዕድሜ ውስጥ ቀለብ አልባ ይሆናሉ" ሲሉ የተማፅኖ ማስጠንቀቂያ አቅርበዋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለም የምግብና እርሻ ድርጅት ከተመድ ማዕከላዊ የአስቸኳይ ድጎማ ግብረምላሽ ለትግራይ ገበሬዎች የማዳበሪያ አቅርቦቱን ከፍ ማድረጊያ የ10 ሚሊየን ዶላር ብድር አግኝቷል።

ፈጣን የብድር አቅርቦቱን አስመልክቶም የዓለም ምግብ ፕሮግራም የምሥራቅ አፍሪካ ንዑስ ሪጂን አስተባባሪና ለኢትዮጵያ ጊዜያዊ ተወካይ ዲቪድ ፊሪ ለለጋሽ ድርጅቱ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

አክለውም፤ ገበሬዎቹ የሚያሹትን ግብዓት በወቅቱ ካገኙ ለማምረትና ምርታቸውንም ከኦክቶበር 2022 ጀምሮ ለመጠቀም እንደሚችሉና ምርቱም ቢያንስ ለስድስት ወራት ፍላጎታቸውን ሊሸፍን እንደሚያስችላቸው አመላክተዋል።







Share

Published

By Kassahun Seboqa Negewo
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service
የዓለም ምግብ ድርጅት አስቸኳይ የገንዘብ እርዳታ ካላገኘ 750,000 ኢትዮጵያ ያሉ ስደተኞች 'የሚበሉት አይኖራቸውም' ሲል አሳሰበ | SBS Amharic