ቻይና በተኩስ የታጀበ የታይዋን ባሕረ ሰላጤ የጦር እንቅስቃሴዋን አበቃች

በፕሬዚደንታዊ ድምፅ አሰጣጥ የማጭበርበር ድርጊት ጥርጣሬ ሳቢያ አንድ የኬንያ መዲና ምርጫ ጣቢያ በጊዜያዊነት ተዘጋ

China - Taiwan tenstions.jpg

China has held drills around Taiwan in response to a recent visit by US House of Representatives Speaker Nancy Pelosi. Credit: AAP / AP / Lin Jian

ቻይና በተኩስ የታጀበ ወታደራዊ እንቅስቃሴዋን ማብቃቷን አስታወቀች።

የወታደራዊውን እንቅስቃሴ ማክተም ያስታወቀው የቻይና ምሥራቅ ዕዝ የወታደሮቹን የውጊያ ብቃት "በብርቱ ፈትኖ" ያበቃ በመሆኑ የጦር ልምምዱን መግታቱን ገልጧል።

የታይዋን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ግና ቻይና ያካሔደችው የጦር ልምምድ ደሴቲቱን ለመውረር የተካሔደ የጦር ዕቅድ መሰናዶ እንደሆነ ተናግረዋል።
 
ይህ በእንዲህ እንዳለም፤ በአውስትራሊያ የቻይና አምባሳደር ሺኦ ችየን በበኩላቸው ቻይና ከታይዋን ጋር ሰላማዊ በሆነ መንገድ ለመዋሃድ የምትሻ መሆኑን ትናንት በአውስትራሊያ ብሔራዊ ፕሬስ ክለብ ባደረጉት ንግግር አመላክተዋል።

***
የኬንያ ፖሊስ በመዲናይቱ ናይሮቢ በአንድ የምርጫ ጣቢያ የድምፅ ማጭበርበር ጥርጣሬ ክስ ደርሶት ባካሔደው ፍተሻ ሳቢያ የማቱጋ ምርጫ ጣቢያ በጊዜያዊነት እንዲዘጋ ተደርጓል።

 ፖሊስ በሥፍራው ደርሶ ባካሔደው ፍተሻ ሁለት ግለሰቦች ሕጋዊ ያልሆኑ አንድ የኤሌክትሮኒክስ ድምፅ መቁጠሪያ፣ የምርጫ ኮሚሽን ማኅተምና ድምፅ ያልተሰጠባቸውን የድምፅ መስጫ ወረቀቶችን ይዘው ተገኝተዋል።

ሁለቱ ተጠርጣሪ ግለሰቦች ወደ ኪዋሊ ፖሊስ ጣቢያ ተወስደው በቁጥጥር ስር እንዲውሉ ተደርጓል።

በመሪነት ላይ በሚገኙት ሁለት ዕጩ ፕሬዜደንቶች ራይላ ኦዲንጋና ዊሊያም ሩቶ መካከል ተቀራራቢ ውጤቶች በኬንያ ዋነኛ ብዙኅን መገናኛዎች እየተገለጡ ነው። ሆኖም የውጤት መግለጫዎቻቸው የተለያዩ ናቸው።
Kenya's Presidential election.jpg
Kenya's Deputy-President and Presidential candidate for Kenya first, William Ruto (L) and, One Kenya Coalition Party presidential candidate Raila Odinga (R). Credit: SIMON MAINA/AFP via Getty Images) / Ed Ram/Getty Images

የኬንያ ምርጫ ኮሚሽን ሐሙስ ጠዋት የቅድሚያ ምርጫ ውጤት ሪፖርቱን ይፋ እንደሚያደርግ ገልጧል።

 





 


Share

Published

By NACA, Kassahun Seboqa Negewo
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service