የሕዝብ አስተያያት ስብስብ በጅሮንድ ጆሽ ፍራይደንበርግ የኩዮንግ ምክር ቤት ወንበራቸውን ሊያጡ እንደሚችሉ እየጠቆመ ነው

*** የግል ተወዳዳሪዎች በተለይም የሊብራል ምክር ቤት አባላት ተወካይ ሆነው ባሉባቸው የከተማና የገጠር የምርጫ ጣቢያዎች ብርቱ ፉክክሮችን እያካሄዱ ነው።

News

Dr Monique Ryan (L) አንድ Treasurer Josh Frydenberg (R)። Source: AAP

በጅሮንድ ጆሽ ፍራይደንበርግ የሜልበርን ኩዮንግ ምክር ቤት ወንበራችውን በግል ተወዳዳሪዋ ዶ/ር ሞኒክ ራያን ሊያጡ እንደሚችሉ የሕዝብ አስተያየት ስብስብ እያመለከተ ነው። 

በሕዝብ አስተያየቱ መሠረት ሞኒክ ራያን ጆሽ ፍራይደንበርግን 53 ለ 47 እየመሩ ነው። 

ዘ አውስትራሊያን ጋዜጣ በዮ ጋቭ ድርጅት በኩል ባሰባሰበው ተጨማሪ የሕዝብ አስተያየት የግል ተወዳዳሪዋ ዞዊ ዳንኤል የሊብራል ፓርቲ ጎልድስታይን ምክር ቤት አባል ቲም ዊልሰንን እየመሩ ይገኛሉ።  

የግል ተወዳዳሪዎች የኒው ሳውዝ ዌይልስ ሊብራል ምክር ቤት አባላት ይዘዋቸው ባሉት የምክር ቤት ወንበሮች ማኪላር፣ ዌንትዎርዝና ሰሜን ሲድኒ ብርቱ ፉክክሮችን እያካሔዱ ነው።  

በተለያዩ ክፍለ አገራትም እንዲሁ የገጠርና የከተማ ምክር ቤት ወንበሮችን ለመያዝ የግል ተወዳዳሪዎች በተቀናቃኝነት ቀርበዋል።  

 

 

 

 

 

 

 

 

 


1 min read

Published

By NACA

Presented by Kassahun Seboqa Negewo


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now