በአውስትራሊያና ኒውዚላንድ አስተናጋጅነት በሚካሔደው የ2023 ፊፋ የዓለም ዋንጫ ዛሬ ነሐሴ 6 በብሪስበን ላንግ ፓርክ ስታዲየም አውስትራሊያና ፈረንሳይ ባደረጉት የሩብ ፍፃሜ ግጥሚያ የሙሉ መደበኛ 90 ደቂቃና ተጨማሪ 30 ደቂቃ ባዶ ለባዶ ተለያይተዋል።
ግጥሚያው ጥሎ ማለፍ በመሆኑም በፍፁም ቅጣምት እንዲለያዩ በመደረጉ አውስትራሊያ ፈረንሳይን 7 ለ 6 በሆነ እጅግ ልብ ሰቃይ ውጤት በማሸነፍ ለቀጣዩ ግማሽ ፍፃሜ ጥሎ ማለፍ አልፋለች።

አውስትራሊያ በቀጣዩ የግማሽ ፍፃሜ ጥሎ ማለፍ ግጥሚያ ረቡዕ ነሐሴ 10 የምትጫወተው ዛሬ ምሽት ከሚፋለሙት እንግሊዝና ኮሎምቢያ አሸናፊ ጋር ይሆናል።
ቀደም ሲል ኔዘርላንድስን 2 ለ 1 የረታችው ስፔይንና ጃፓንን በተመሳሳይ ውጤት ጃፓንን 2 ለ 1 ድል የነሳችው ስዊድን ማክሰኞ ነሐሴ 9 አመሻሽ ላይ ለፍፃሜ ዋንጫ ለመቅረብ ብርቱ ፉክክር ያካሂዳሉ።

