Watch FIFA World Cup 2026™

LIVE, FREE and EXCLUSIVE

አውስትራሊያ ፈረንሳይን በፍፁም ቅጣት ምት ብልጫ ረትታ ለዓለም ዋንጫ ግማሽ ፍፃሜ አለፈች

አውስትራሊያ በሴቶች እግር ኳስ ለዓለም ዋንጫ ለግማሽ ፍፃሜ ስታልፍ ይህ የመጀመሪያ ጊዜዋ ነው።

Matildas.jpg
Sam Kerr came on for the Matildas in the 55th minute, hoping to break the deadlock. Credit: AAP / Jono Searle

በአውስትራሊያና ኒውዚላንድ አስተናጋጅነት በሚካሔደው የ2023 ፊፋ የዓለም ዋንጫ ዛሬ ነሐሴ 6 በብሪስበን ላንግ ፓርክ ስታዲየም አውስትራሊያና ፈረንሳይ ባደረጉት የሩብ ፍፃሜ ግጥሚያ የሙሉ መደበኛ 90 ደቂቃና ተጨማሪ 30 ደቂቃ ባዶ ለባዶ ተለያይተዋል።

ግጥሚያው ጥሎ ማለፍ በመሆኑም በፍፁም ቅጣምት እንዲለያዩ በመደረጉ አውስትራሊያ ፈረንሳይን 7 ለ 6 በሆነ እጅግ ልብ ሰቃይ ውጤት በማሸነፍ ለቀጣዩ ግማሽ ፍፃሜ ጥሎ ማለፍ አልፋለች።

France.jpg
France players show dejection after the team's defeat through the penalty shoot-out following the FIFA Women's World Cup Australia & New Zealand 2023 Quarter Final match between Australia and France at Brisbane Stadium on August 12, 2023, in Brisbane / Meaanjin, Australia. Credit: Quinn Rooney/Getty Images

አውስትራሊያ በቀጣዩ የግማሽ ፍፃሜ ጥሎ ማለፍ ግጥሚያ ረቡዕ ነሐሴ 10 የምትጫወተው ዛሬ ምሽት ከሚፋለሙት እንግሊዝና ኮሎምቢያ አሸናፊ ጋር ይሆናል።

ቀደም ሲል ኔዘርላንድስን 2 ለ 1 የረታችው ስፔይንና ጃፓንን በተመሳሳይ ውጤት ጃፓንን 2 ለ 1 ድል የነሳችው ስዊድን ማክሰኞ ነሐሴ 9 አመሻሽ ላይ ለፍፃሜ ዋንጫ ለመቅረብ ብርቱ ፉክክር ያካሂዳሉ።


1 min read

Published

Updated

By Kassahun Seboqa Negewo

Source: SBS


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now