አውስትራሊያና ፓፑዋ ኒው ጊኒ ዛሬ የሁለትዮሽ ፀጥታ ስምምነት ሊፈራረሙ ነው

ሩስያ የዩክሬይንን ጦርነት የሚመሩ አዲስ ጄኔራል ሾመች።

Aust PNG.jpg

Flags of Australian (L) and PNG (R). Credit: Tracey Nearmy/Getty Images James D. Morgan/Getty Images)

ጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልባኒዚ ዛሬ ጥር 4 ፓፕዋ ኒው ጊኒ ተገኝተው የሁለትዮሽ የፀጥታ ስምምነት ፊርማ ያኖራሉ።

አቶ አልባኒዚ በታሪካዊነቱ የመጀመሪያው የውጭ አገር መሪ በመሆንም ለፓፕዋ ኒው ጊኒ ፓርላማ ንግግር ያሰማሉ።

በንግግራቸውም የሁለቱን አገራት ፀጥታ ደረጃ፣ ምጣኔ ሃብታዊ ግንኙነት፣ በአየር ንብረት ለውጥ፣ ትምህርት፣ ባዮሴኩሪቲና መሠረተ ልማት ዙሪያ ያለውን ትብብር ከፍ ስለማድረግ እንደሚያነሱ ከወዲሁ ፍንጭ ሰጥተዋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለም፤ የስደተኞች መብቶች ተሟጋቾች ጠቅላይ ሚኒስትር አልባኒዚ ፓፕዋ ኒው ጊኒ ውስጥ ያሉ ጥገኝነት ጠያቂዎችን በሙሉ ከዚያ እንዲያስወጡ ጠይቀዋል።

በ2013 ማኑስ ደሴት ከነበሩ ከከ1,000 በላይ ጥገኝነት ጠያቂዎች ውስጥ በአሁኑ ወቅት 90 ጥገኝነት ጠያቂዎች ፓፕዋ ኒው ጊኒ ውስጥ ይገኛሉ።

በርካቶቹም ለአዕምሮ ሕመምና ለአካላዊ ጤንነት መታወክ ተጋልተው ያሉ መሆናቸውንም የስደተኞች መብቶች ተሟጋቾቹ አመልክተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር አልባኒዚ ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት ፓፕዋ ኒው ጊኒ ገብተዋል።

ሩስያ

ሩስያ የዩክሬይንን ጦርነት የሚመሩ አዲስ ጄኔራል ሾመች።

ቀደም ሲል የዩክሬይን ጦርነትን እንዲመሩ ሾማቸው የነበሩትን ጄኔራል ሰርጌይ ሱሮቪኪን ከሶስት ወራት የአመራር ኃላፊነት በኋላ በጄኔራል ቫሌሪ ገራሲሞቭ መተካቷን የሩስያ መከላከያ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።

አክሎም ከዋና አዛዥነታቸው የተነሱትና ከኪኸርሰን ያፈገፈጉት ጄኔራል ሱሮቪኪን በምክትል አዛዥነት እንደሚቀጥሉ ገልጧል።


 




 





Share

Published

By NACA, Kassahun Seboqa Negewo
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service