በዛሬው የአገራዊ ምርጫ ዘመቻ ጠ/ሚ ስኮት ሞሪሰን በአዕምሮ ጤና፤ የሌበር መሪ አልባኒዚ የዝቅተኛ ደመወዝ ጭማሪ ላይ አተኩረው ውለዋል

*** በአውስትራሊያ የቻይና አምባሳደር 'ቻይና ለአውስትራሊያ ስጋት አይደለችም' አሉ፤ የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰለሞን ደሴቶችን ሊጎበኙ ነው።

News

Leader of the Opposition Anthony Albanese (L) and Australian Prime Minister Scott Morrison. Source: Getty

የፌዴራል መንግሥቱ ለአዕምሮ ጤና ግልጋሎት መስጪያ የሚሆን የ$55 ሚሊየን የሽርክና ስምምነት ከታዝማኒያ መንግሥት ጋር ተፈራርሟል።

በስምምነቱ መሠረት $46 ሚሊየን ዶላርስ ወጪ በፌዴራል መንግሥቱ የሚሸፍን ይሆናል።

ገንዘቡ ሶስት የአዕምሮ ጤና ክሊኒኮችን በርኒ፣ ደቮንፖርትና ሆባርት መውጫ ላይ ለማቋቋሚያነት ይውላል። 

                                                          

 

ምርጫ ዝቅተኛ ደመወዝ

 

የፌዴራል በጅሮንድ ጆሽ ፍራይደንበርግ የተቃዋሚ ቡድን ፓርቲ የምጣኔ ሃብት ፖሊሲያቸው ግብታዊነት ላይ እንጂ በዕቅድ የተያዘ ፖሊሲ አይደለም በማለት ተችተዋል።

አቶ አልባኒዚ የዝቅተኛ ደመወዝ ማስተካከያ ከወቅቱ የዋጋ ግሽበት ጋር መመጣጠን እንዲችል የ 5.1 ፐርሰንት ጭማሪ እንዲደረግ የሚሹና ለፍትሐዊ የሥራ ኮሚሽንም ይህንኑ አስመልክተው በፅሁፍ እንደሚያቀርቡ ተናገረዋል። 

ሆኖም አቶ ፍራይደንበርግ የመንግሥታቸው አቋም ጉዳዩን ለኮሚሽኑ መተው እንደሆነ ገልጠዋል።

በሌላ በኩል የአውስትራሊያ አገር አቀፍ የሠራተኞች ማኅበር የዝቅተኛ ደመወዝ ጭማሪ 5.5 ፐርሰንት እንዲሆን የሚሻ ሲሆን፤ የንግዱ ማኅበረሰብ ቡድን ጭማሪው ከሶስት ፐርሰንት እንዳያልፍ ይፈልጋል።

ቻይና - አውስትራሊያ - ሰለሞን ደሴቶች

በአውስትራሊያ የቻይና አምባሳደር ሺያዎ ቺያን ዛሬ ሐሙስ በአውስትራሊያን ፋይናንሻል ሪቪው ጋዜጣ ላይ ለህትመት ባበቁት መጣጥፋቸው አገራቸው ከፓስፊክ ደሴት አገራት ጋር  የምታደርገው ትብብር ለአውስትራሊያ ስጋት አለመሆኑን አስፍረዋል። 

ሆኖም ጠቅላይ ሚኒስትር ስኮት ሞሪሰን ዋናው ጉዳይ ቻይና የምትለው ሳይሆን የምታደርገው ነው በማለት አሌ ብለውታል። 

 

ይህ በእንዲህ እንዳለም፤ የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በሚቀጥለው ሳምንት ሰለሞን ደሴቶችን እንደሚጎበኙ ተነግሯል።  

 

 

 


Share

Published

Updated

By NACA
Presented by Kassahun Seboqa Negewo

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service