የሌበር ፓርቲ 'የአስቸኳይ ክብካቤ' ክሊኒኮች ላይ ሲያተኩር ሊብራል ፓርቲ የነዳጅ አቅርቦት ላይ አተኩሯል

*** የግሪንስ ፓርቲ በዘንድሮ ምርጫ የፓርላማ ኃይል ሚዛን ለማግኘት ከበቃ ለሁሉም አውስትራሊያውን በሜዲኬይር የሚሸፈን የጥርስ ክብካቤ የሚያስገኝ ፖሊሲውን ይፋ አደረገ።

News

Opposition leader Anthony Albanese. Source: AAP

የተቃዋሚ ቡድን መሪ አንቶኒ አልባኒዚ በሜዲኬይር የሚደጎሙ የሙከራ 50 የአስቸኳይ የጤና ክሊኒኮች በመላ አውስትራሊያ ግብር ላይ እንደሚያውሉ አስታወቁ። 

ክሊኒኮቹ ግብር ላይ እንዲውሉ የሚደረጉት በሆስፒታል ያሉ የድንገተኛ አስቸኳይ ዲፓርትመንቶችን መጨናነቅ በመቀነስ ለቤተሰቦች የተሻለ አማራጭ የሕክምና ግልጋሎቶችን መስጠት ያስችላሉ ከሚል ዕሳቤ ነው።  

የሚያተኩሩባቸው የሕክምና ግልጋሎት ዘርፎችም የአጥንት ስብራት፣ አንስተኛ የአካል ቃጠሎና የተቆረጠ የሰውነት ክፍልን መስፋት ናቸው። 

ለአስቸኳይ የጤና ክሊኒኮቹ መደጎሚያ በአራት ዓመታት ውስጥ $135 ሚሊየን ዶላርስ በጀት የሚመደብላቸው ይሆናል። 

አቶ አልባኒዚ የክሊኒኮቹ ግልጋሎቶች ሜዲኬርን የማጠናከሪያ እርምጃም እንደሆነ አስታውቀዋል።

ነዳጅ

ጠቅላይ ሚኒስትር ስኮት ሞሪሰን ለድፍድፍ ነዳጅ ማጣሪያ የሚውል $250 ሚሊየን መመደባቸውን አስታወቁ። 

ከበጀቱ ውስጥ $125 ሚሊየን ዶላር ለቪቫ ኢነርጂ እና አምፖል ድፍድፍ ነዳጅ ማጣሪያ ኩባንያዎች በጥሬ ገንዘብ ለድጎማ የሚውል ይሆናል።
News
Prime Minister Scott Morrison meets refinery workers during a visit to Geelong Oil Refinery on Day 3 of the 2022 federal election campaign. Source: AAP
አቶ ሞሪሰን ጂሎንግ ከኢነርጂ ሚኒስትር አንገስ ቴይለር ጋር ሆነው ሲናገሩ፤ ድጎማው ለአውስትራሊያ የወደፊት የነዳጅ አቅርቦት ዋስትና እንደሚበጅና ተጨማሪ የሥራ ዕድልም እንደሚፈጥር ተናግረዋል። 

ተጨማሪው $125 ሚሊየን ዶላር ለኩዊንስላንድ የተመደበ መሆኑን ገልጠዋል። 

የጥርስ ሕክምና

የግሪንስ ፓርቲ መሪ አደም ባንድት በዘንድሮው ምርጫ ፓርላማ ውስጥ የኃይል ሚዛን ለማግኘት ከበቃ ከ$77 ቢሊየን በላይ በአንድ አሠርት ዓመት የሚያወጣ የጥርስ ክብካቤ ዕቅድ እንዳላቸው ይፋ አድርገዋል። 

ዕቅዱ አውስትራሊያውያን በሜዲኬይር የሚሸፈን የጥርስ ክብካቤ ሕክምና እንዲያገኙ የሚያደርግ መሆኑን በመግለፅ የፓርቲያቸውን ፖሊሲ ገልጠዋል።
Greens leader Adam Bandt addresses the National Press Club in Canberra on Wednesday
Greens leader Adam Bandt addresses the National Press Club in Canberra on Wednesday. Source: AAP
አክለውም፤ ባለፈው ወቅት ግሪንስ የኃይል ሚዛን ይዞ በነበረበት ወቅት ለልጆች የጥርስ ሕክምና ከሜዲኬይር ጋር እንዲያያዝ ማስደረግ መቻሉን ጠቁመው ዘንድሮም ፓርቲያቸው ዕድሉ ከገጠመው በሜዲኬይር የሚሸፈን የጥርስ ክብካቤ ለሁሉም ለማስገኘት እንደሚያደርግ ተናግረዋል።   


ዋን ኔሽን ፓርቲ

የቀድሞው የኩዊንስላንድ ሊብራል ናሽናል የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል ጆርጅ ክሪስቴንሰን በዘንድሮው የሜይ 21 አገር አቀፍ ምርጫ ዋን ኔሽን ፓርቲን ወክለው እንደሚወዳደሩ አስታወቁ። 

አቶ ክሪስቴንሰን በዚህ ወር መጀመሪያ ላይ ከሊብራል ናሽናል ፓርቲ አባልነታቸው የለቀቁ ሲሆን፤ ከዳውሰን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባልነታቸው በዚህ ወር መጨረሻ የሚለቁ ይሆናል።
News
One Nation leader Pauline Hanson and her new Senate candidate George Christensen. Source: AAP
አቶ ክሪስቴንሰን በዘንድሮው ምርጫ ዋን ኔሽንን ወክለው የሚወዳደሩት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ይሁን ወይም ለሕግ መወሰኛ ምክር ቤት መሆኑ አልተገለጠም። 




 


Share

Published

By NACA
Presented by Kassahun Seboqa Negewo

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service