SKIP TO MAIN CONTENT

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ለአረንጓዴ ዐሻራ ንቅናቄ መሪ አስተዋፅዖ “የአፍሪካ የላቀ አመራር” ሽልማት ተበረከተላቸው

ሽልማቱ የተበረከተላቸው “አፍሪካ የዓለም አቀፍ ንቅናቄ አጣዳፊነት” በሚል መሪ ሐሳብ አሜሪካን አካዳሚ ኦፍ አቺቭመንት እና ግሎባል ሆፕ ኮአሊሽን የተሰኙ ተቋማት በዋሽንግተን ዲሲ በጋራ ባዘጋጁት ልዩ ዝግጅት ላይ መሆኑን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት አሳውቋል፡፡

PM Abiy Ahmed.jpg
Ethiopian Prime Minister Abiy Ahmed received the ‘Outstanding African Leadership Award’ in recognition of the Green Legacy Initiative on December 13, 2022, in Washington, DC. Credit: PMOE

1 min read

Published

By Stringer Report

Source: SBS


Skip to article content

ጽሕፈቱ በማሕበራዊ ትስስር ገፁ እንዳሰፈረው ኢትዮጵያ በ2011 ዓ.ም. የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብርን ስታስጀምር፣ በአራት ዓመታት ውስጥ 20 ቢልየን ችግኞችን ለመትከል ማቀዷ ይታወሳ ብሏል፡፡

ጽሕፈት ቤቱ ኢትዮጵያ ከታቀደው ግብ አልፋ በመላ ሀገሪቱ 25 ቢልየን ችግኞች በመትከል የአራት ዓመት ዕቅዷን አሳክታለች ሲልም አክሏል።

በዚህም የአየር ንብረት ለውጥን ለመቅረፍ እና ለደን መልሶ ልማት ላደረገችው አስተዋጽዖ በዓለም አቀፍ ደረጃ ዕውቅና አግኝታለች ብሏል።


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Stream now