የአውስትራሊያ መንግሥት በጊዜያዊ ቪዛ ያሉ 19 ሺህ ነዋሪዎች ከዛሬ ጀምሮ ለቋሚ ቪዛ እንዲያመለከቱ ፈቀደ

የብሔራዊ ይቅርታ ቀን 15ኛ ዓመት ካንብራ ላይ ተከበረ

Immigration Minister Andrew Giles.jpg

Immigration Minister Andrew Giles. Credit: AAP / Lukas Coch

ከዛሬ ሰኞ ፌብሪዋሪ 13 / የካቲት 6 አንስቶ የአውስትራሊያ መንግሥት በጊዜያዊ ቪዛዎች ያሉ ነዋሪዎች ለቋሚ ቪዛ ማመልከት እንደሚችሉ አስታወቀ።

የኢሚግሬሽን ሚኒስትር አንድሩ ጂለስ በተለይ በጊዜያዊ ቪዛ ያሉ ነዋሪዎች ለ10 ዓመታት እርግጠኝነት አልባ በሆነ ሁኔታ ውሳኔን ሲጠብቁ እንደቆዩ አመላክተዋል።

ለቋሚ ቪዛ ማመልከት የሚችሉት የሉዓላዊ ድንበሮች ዘመቻ ድንጋጌ ግብር ላይ ከመዋሉ በፊት ወደ አውስትራሊያ የዘለቁ ባለ ጊዜያዊ ቪዛ ባለቤቶችን ነው።

ማመልከቻቸውን አስገብተው ቋሚ ቪዛ የሚያገኙ ሰዎች ቋሚ ቪዛ ያላቸው ነዋሪዎች የሚያገኟቸውን መብቶችና ጥቅሞች ሁሉ የሚያገኙ ይሆናል።

ይህ በእንዲህ እንዳለም፤ ጉዳያቸው ታይቶ ጥበቃ ለማግኘት ብቁ ያልሆኑና የአቤቱታ ክለሳ የማይጠብቁ ግለሰቦች አውስትራሊያን ለቅቀው እንዲወጡ የሚደረግ መሆኑን የአገር ውስጥ ጉዳዮች ሚኒስትር ክሌየር ኦኒል አስታውቀዋል።

ብሔራዊ ይቅርታ

የተሰረቁ ትውልዶችን አስመልክቶ የተካሔደው ብሔራዊ የይቅርታ ቀን ዛሬ ሰኞ ፌብሪዋሪ 13 / የካቲት 6 በመዲናይቱ ካንብራ በቁርስ ሥነ ሥርዓት ታስቧል።

በ2008 የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር ኬቨን ራድ የአውስትራሊያ ነባር ዜጎች ባለፉት መንግሥታት ሕፃናትን ከወላጆች የመነጠል ፖሊሲዎች ሳቢያ ለመንፈስ ጭንቀትና ጥበት መዳረግን አስመልክቶ ብሔራዊ ይቅርታን ጠይቀዋል።

ይህንኑ አስመልክቶ ሴናተር ፓት ዶድሰን ለABC በሰጡት መግለጫ ብሔራዊ ይቅርታው የቁርሾ ፈውስ ጅማሮ መሆኑን ገልጠዋል።

Share

Published

By Kassahun Seboqa Negewo, NACA
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service