Watch FIFA World Cup 2026™

LIVE, FREE and EXCLUSIVE

የአውስትራሊያ መንግሥት በጊዜያዊ ቪዛ ያሉ 19 ሺህ ነዋሪዎች ከዛሬ ጀምሮ ለቋሚ ቪዛ እንዲያመለከቱ ፈቀደ

የብሔራዊ ይቅርታ ቀን 15ኛ ዓመት ካንብራ ላይ ተከበረ

Immigration Minister Andrew Giles.jpg

Immigration Minister Andrew Giles. Credit: AAP / Lukas Coch

ከዛሬ ሰኞ ፌብሪዋሪ 13 / የካቲት 6 አንስቶ የአውስትራሊያ መንግሥት በጊዜያዊ ቪዛዎች ያሉ ነዋሪዎች ለቋሚ ቪዛ ማመልከት እንደሚችሉ አስታወቀ።

የኢሚግሬሽን ሚኒስትር አንድሩ ጂለስ በተለይ በጊዜያዊ ቪዛ ያሉ ነዋሪዎች ለ10 ዓመታት እርግጠኝነት አልባ በሆነ ሁኔታ ውሳኔን ሲጠብቁ እንደቆዩ አመላክተዋል።

ለቋሚ ቪዛ ማመልከት የሚችሉት የሉዓላዊ ድንበሮች ዘመቻ ድንጋጌ ግብር ላይ ከመዋሉ በፊት ወደ አውስትራሊያ የዘለቁ ባለ ጊዜያዊ ቪዛ ባለቤቶችን ነው።

ማመልከቻቸውን አስገብተው ቋሚ ቪዛ የሚያገኙ ሰዎች ቋሚ ቪዛ ያላቸው ነዋሪዎች የሚያገኟቸውን መብቶችና ጥቅሞች ሁሉ የሚያገኙ ይሆናል።

ይህ በእንዲህ እንዳለም፤ ጉዳያቸው ታይቶ ጥበቃ ለማግኘት ብቁ ያልሆኑና የአቤቱታ ክለሳ የማይጠብቁ ግለሰቦች አውስትራሊያን ለቅቀው እንዲወጡ የሚደረግ መሆኑን የአገር ውስጥ ጉዳዮች ሚኒስትር ክሌየር ኦኒል አስታውቀዋል።

ብሔራዊ ይቅርታ

የተሰረቁ ትውልዶችን አስመልክቶ የተካሔደው ብሔራዊ የይቅርታ ቀን ዛሬ ሰኞ ፌብሪዋሪ 13 / የካቲት 6 በመዲናይቱ ካንብራ በቁርስ ሥነ ሥርዓት ታስቧል።

በ2008 የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር ኬቨን ራድ የአውስትራሊያ ነባር ዜጎች ባለፉት መንግሥታት ሕፃናትን ከወላጆች የመነጠል ፖሊሲዎች ሳቢያ ለመንፈስ ጭንቀትና ጥበት መዳረግን አስመልክቶ ብሔራዊ ይቅርታን ጠይቀዋል።

ይህንኑ አስመልክቶ ሴናተር ፓት ዶድሰን ለABC በሰጡት መግለጫ ብሔራዊ ይቅርታው የቁርሾ ፈውስ ጅማሮ መሆኑን ገልጠዋል።


1 min read

Published

By Kassahun Seboqa Negewo, NACA

Source: SBS


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now