ኢትዮ-ቴሌኮም ከ64 ሚሊየን ዶላር በላይ ገቢ ማስገኘቱንና የደንበኞቹ ቁጥር 70 ሚሊዮን መድረሳቸውን አስታወቀ

ኢትዮ-ቴሌኮም በ2014 በጀት ዓመት ዘጠኝ ቢሊየን ብር የተጣራ ትርፍ ሲያገኝ፤በ2015 የበጀት ዓመት በስድስት ወራት ብቻ 8.18 ቢሊየን ብር የተጣራ ትርፍ አግኝቷል።

Frehiwot Tamiru.jpg

Frehiwot Tamiru, CEO of Ethio-Telecom. Credit: Ethio-Telecom

የኩባንያው ዋና ሥራ አስፈፃሚ ወ/ሪት ፍሬህይወት ታምሩ የተቋሙን የስራ አፈጻጸም በተመከከተ ባቀረቡት ማብራሪያ እንደተናገሩት ባለፈው ስድስት ወራት ድርጅቱ ለውድድሩ ገበያ ብቁ እንዲሆን የኔትወርክ ማስፋፊያ ብሎም የማኅበረሰቡን አቅም ታሳቢ ያደረገ ታሪፍ የያዘ ስትራቴጂ ቀርጾ ስራ ሲሰራ መቆየቱን ገልፀዋል።

የሶስት ዓመት ስትራቴጂ በዋናነት መሪ ዲጂታል መፍትሄዎች አቅራቢ፣ ከፍተኛ የደንበኛ ልምድ፣ ቀጣይነት ያለው የንግድ ዕድገት፣ በቴክኖሎጂ እና መፍትሄዎች የላቀ፣ የተግባር ልቀት ያለው ባለሙያዎችን ያማከለ በመሆን ከፍተኛ አፈጻጸም ያለው ኩባንያ እንዲሆን ማድረግ መቻሉንም ፍሬህይወት ተናግረዋል።

ኢትዮቴሌኮም ለSBS ባደረሰው መረጃ ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ እሴትን ይጨምራሉ የተባሉ ሥራዎችን ባለፉት ስድስት ወራት የተሰራ ሲሆን፤ በዚህም የደንበኞች ብዛት ወደ 70 ሚሊዮን እንዲደርስ ማድረግ ተችሏል ብሏል።

67.7 ሚሊዮን ደንበኞች የድምጽ ጥቅል ተጠቃሚ መሆናቸውን የገለፀው ኩባንያው ባለፉት ስድስት ወራት ኩባንያው 9.2 ሚሊዮን ተጨማሪ ደንበኞች ማፍራት በመቻሉ ይህ አፈፃፀሙ የእቅዱን 99.9 በመቶ ማሳካት እንዳስቻለው ገልጿል።

ኢትዮ-ቴሌኮም በ2014 በጀት ዓመት ዘጠኝ ቢሊየን ብር የተጣራ ትርፍ ማግኘቱን ገልፆ በያዝነው በጀት ዓመት ስድስት ወራት ብቻ 8.18 ቢሊየን ብር የተጣራ ትርፍ ማግኘቱን ገልጧል።

ለትርፍ እድገቱ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያደረገውም ኩባንያው የተገበረው የወጪ ቅነሳ ስራ እንደሆነ አክሎ አስታውቋል።

ኢትዮ-ቴሌኮም በወጪ ቅነሳ 3.5 ቢሊየን ብር ለማዳን የቻለ ሲሆን፤ በመጀመሪያው መንፈቅ ዓመት 33.8 ቢሊየን ብር ገቢ አግኝቷል። በዚህም የእቅዱን 96 በመቶ ማሳካት መቻሉን ገልፀዋል።

ገቢው ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ20 በመቶ የ5.62 ቢሊየን ብር ዕድገት ማሳየቱን የገለፀው ኩባንያው 91 አዳዲስ እና የተሻሻሉ አገልግሎቶች አቅርቧል።

በውጪ ምንዛሪ 64.8 ሚሊየን ዶላር ገቢ ማስገባቱ ተገልጿል።

[ ደመቀ ከበደ ፡ አዲስ አበባ ]

Share

Published

Updated

By Demeke Kebede
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service