የ2023/2015 ሉላዊ ወታደራዊ ኃይል ጥንካሬ አሰላለፍን ዩናይትድ ስቴትስ፣ሩስያና ቻይና በቀዳሚነት እየመሩ ነው

ኢትዮጵያ በ2023 ከአፍሪካ 38 አገራት በወታደራዊ ኃይል ጥንካሬ አምስተኛ ከዓለም 49ኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች።

The F-22 Raptor.jpg

The F-22 Raptor. It is the US Air Force's next-generation air dominance fighter being designed and manufactured under a joint project funded by numerous defence contractors and foreign governments. Credit: Mai/Getty Images

በዘንድሮው 2023 / 2015 ሉላዊ የወታደራዊ ኃይል ጥንካሬ ምደባ ከ145 የዓለም አገራት ውስጥ ዩናይትድ ስቴትስ፣ ሩስያ፣ ቻይና፣ሕንድ፣ እንግሊዝ፣ ደቡብ ኮሪያ፣ ፓኪስታን፣ ጃፓን ፈረንሳይና ጣሊያን በቅደም ተከል ከአንደኛ እስከ አሥረኛ ያለውን ደረጃ ይዘዋል።

አውስትራሊያ ከዓለም 16ኛ ሥፍራን ስትይዝ ከ145ቱ አገራት የመጨረሻው የኃይል ሰእንጠረዥ ላይ የሠፈረችው የደቡብ እስያይቷ ብሁታን ናት።

ከአፍሪካ በወታደራዊ ኃይል ጥንካሬያቸው ግብፅ፣ አልጀሪያ፣ደቡብ አፍሪካ፣ ናይጄሪያ፣ ኢትዮጵያ፣ አንጎላ፣ ሞሮኮ፣ ዲሞክራሲያዊት ኮንጎ፣ አንጎላና ሱዳን በቅደም ተከተል ከአንደኛ እስከ አሥረኛ ተመድበዋል።

ከ38ቱ የአፍሪካ አገራት በወታደራዊ ጥንካሬዋ የመጨረሻው ሠንጠረዥ ላይ ያረፈችው ቢኒን ናት።

በመካከለኛው ምሥራቅና ሰሜን አፍሪካ የወታደራዊ ኃይል ምደባ ዘርፍ ቱርክ፣ ግብፅ፣ ኢራን፣ እሥራኤል፣ ሳኡዲ አረቢያ፣ አልጄሪያ፣ ኢራቅ፣ የተባበሩት ዓረብ ኢምሬት ፣ ሞሮኮና ሶሪያ ከአንደኛ እስከ አሥረኛ የቅደም ተከተል ሥፍራ ይዘዋል።

ከ20 የመካከለኛውና ሰሜን አፍሪካ አገራት የመጨረሻው እርከን ላይ የተመደበችው ሊባኖስ ናት።

የወታደራዊ ኃይል ጥንካሬ ደረጃ ምደባው የተካሔደው በግሎባል ፋየርፓወር አማካይነት ሲሆን፤ የደረጃ ምደባ አንኳር መመዘኛውን ያደረገውም የአገራቱን የወታደራዊ ክፍሎች ጥንካሬ፣ የፋይናንስ ቁመናና የወታደራዊ ቁሳቁሶች ብቃትና ጂኦግራፊን ከግምት ውስጥ በማስገባት ነው።

የወታደራዊ ልዕለ ኃይል የላቀ ሠንጠረዥ ደረጃ 0.0000 ሲሆን አንዳቸውም የዓለም አገራት ከዚያ ደረጃ ላይ አልደረሱም።

የዓለም ገናናዎቹ አገራት የወታደራዊ ልዕለ ኃይል የላቀ ሠንጠረዥ ደረጃ መሠረት ዩናይትድ ስቴትስ 0.0712፣ ሩስያ 0.0714 ቻይና 0.0722 ሲሆን ከአፍሪካ ግብፅ 0.0224 ኢትዮጵያ 0.07979 ላይ ይገኛል።


Share

Published

Updated

By Kassahun Seboqa Negewo
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service