ጠቅላይ ሚኒስትር ስኮት ሞሪሰን ድጋሚ ከተመረጥኩ "የቡልዶዘር" አመራሬን እለውጣለሁ አሉ

*** የሌበር መሪ አንቶኒ አልባኒዚ "ቡልዶዘር ነገሮችን ያፈርሳል፤ ይገረስሳል። አኔ አገር ገንቢ ነኝ" ብለዋል።

News

Bob the Builder (L), and a Bulldozer (R). Source: Getty

ጠቅላይ ሚኒስትር ስኮት ሞሪሰን ዛሬ ዓርብ በጠሩት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ በመንግሥታዊ አመራራቸው ወቅት "በመጠኑ የቡልዶዘር" አመራርን መተግበር ግድ ይል እንደነበር አመላክተው፤ ሆኖም ዳግም ከተመረጡ የአመራር ስልት ለውጥ እንደሚያደርጉ ገለጡ።

አቶ ሞሪሰን የአመራር ለውጥ ሊያደርጉ እንደሚችሉ የገለጡት አውስትራሊያውያንን ይበልጥ ቀርበው መስማት ያለባቸው እንደሁ በተጠየቁበት ወቅት ነው።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በምላሻቸው "አውስትራሊያውያንን መስማት በጣም ጠቃሚ ነው፤ በፖለቲካ ሙያዬ ወቅት ሁሉ ያንን አድርጌያለሁ"  

 

"ወደ ሁኔታዎች ሲመጣ በመጠኑ ቡልዶዘር መሆን እንደምችል እኔም አውቃለሁ፤ አውስትራሊያውያንም ያውቃሉ" ብለዋል።

 

ይህንኑ የጠቅላይ ሚኒስትሩን አባባል ተከትሎ የሌበር መሪ ፈጥነው በሰነዘሩት ምላሽ፤

 

"ዛሬ ስኮት ሞሪሰን ቡልዶዘር መሆናቸውን ተናግረዋል። ቡልዶዘር ነገሮችን ያፈርሳል፣ ቡልዶዘር ነገሮችን ይገረስሳል። እኔ ገንቢ ነኝ። ያ ነኝ እኔ"

"ጠቅላይ ሚኒስትር ሆኜ ከተመረጥኩ እዚህ አገር ውስጥ ነገሮችን እገነባለሁ። ስኮት ሞሪሰን ለእኔ ድምፅ ስጡ፤ እናም እለወጣለሁ ብለዋል። ለውጥ የምትሹ ከሆነ፤ የመንግሥት ለውጥ አድርጉ" ብለዋል። 


1 min read

Published

Updated

By NACA, kassahun Seboqa


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now