ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ በተመድ ፀጥታ ምክር ቤት የወሲባዊ ጥቃት ዓመታዊ ሪፖርት ውስጥ ተካተተች

***የተመድ ዋና ፀሐፊ ልዩ ወኪል ፕራሚላ ፓቴን የወሲባዊ ጥቃት መረጃዎች ከታይታነት አልፈው ለሕጋዊ ተጠያቂነት የሚበያቁ እንዲሆኑ አሳስበዋል።

News

Pramila Patten, Special Representative of the Secretary, at the United Nations. Source: Getty

የተባበሩት መንግሥታት የፀጥታ ምክር ቤት ትናንት ኤፕሪል 13 ባካሔደው ስብሰባ ወሲባዊ ጥቃትን እንደ ጦር መሣሪያነት መጠቀምን ለማክሰም እየሠሩ ያሉት የተመድ ዋና ፀሐፊ ልዩ ወኪል ፕራሚላ ፓቴን በሥፍራው ተገኝተው ለሰለባዎች ፍትሕን፣ እንዲሁም ወሲባዊ ጥቃትን በቅድሚያ ስለ መከላከል አበክረው ተናግረዋል። 

አክለውም፤ ምክር ቤቱ ሴቶች፣ ሰላምና ፀጥታን አስመልክቶ 10 እንዲሁም ከግጭት ጋር የተያያዙ ወሲባዊ ጥቃቶችን ማመልከትንና ቅድመ መከላከል ማድረግን አስመልክቶ አምስት የአቋም መግለጫዎችን ማሳለፉን አንስተው፤ የእወጃዎቹ እርባና በአሁኑ ወቅት ለዩክሬይን፣ አፍጋኒስታንና ሚያንማር ወይም ለሰሜናዊት ኢትዮጵያ ትግራይ ሴቶች ምን ማለት እንደሆነ ጠይቀዋል። 

ወሲባዊ ጥቃትን እንደ ጦር መሣሪያነት መጠቀምን ያመላክተው ዓመታዊው ሪፖርት የ2020 ጥቃቶችን ያዘለና 18 አገራትን ያካተተ ሲሆን፤ ባለፈው ዓመት 3,293 በተመድ የተረጋገጡ ጥቃቶችንም ይዟል። 

ጥቃቶቹ 97 ፐርሰንት ያህሉ ሴቶችና ልጃገረዶችን ዒላማ ያደረጉ ስለመሆኑ፣ 83 እገታ ማዕከላት ውስጥ ወሲባዊ ጥቃቶች የተፈፀመባቸውን አዋቂና ወጣት ወንዶችን፤ እንዲሁም 12 የተመሳሳይ ፆታ ግንኙነት ያላቸው ሰዎች ላይ የተፈፀሙ መሆናቸውንም ሪፖርቱ አመልክቷል።

ሪፖርቱ የድርጊት ዒላማ ላይ ያነጣጠረ ቅድመ መከላከል ለማድረግ ፖለቲካዊና ዲፕሎማሲያዊ ተሳትፎዎች እንዲካሔዱ፣ ወሲባዊ ጥቃትን በተኩስ አቁምና የሰላም ስምምነቶች ወቅት እንዲነሳ፣ ቅድመ የወሲባዊ ጥቃት ማስጠንቀቂያና ትንተና እንዲደረግ፣ አነስተኛ የጦር መሳሪያ ፍሰትን መገደብ፣ ጾታ ተኮር ፍትሐዊ የአፀፋ እርምጃ እንዲወሰድ፣ የፀጥታ መስክ ማሻሻያ ለውጥና የሰለባዎች ድምፆች ጎልተው እንዲሰሙ ማድረግ የሚሉ ምክረ ሃሳቦችን አያይዞ አቅርቧል።

ወ/ሮ ፓቴንም በበኩላቸው ዶክሜንቶቹ ከታይታነት አልፈው ለሕጋዊ ተጠያቂነት የሚበያቁ እንዲሆኑ አሳስበዋል።   

ይህ በእንዲህ እንዳለም፤ ከኢራቅ፣ ሶሪያና ኢትዮጵያ ሴቶች በኩል ወሲባዊ ጥቃቶችን አስመልክተው እማኝነታቸውን አስደምጠዋል።  

በኢትዮጵያ በኩል ኅሊና ብርሃኑ የትግራይ ጉብኝታቸውን አንስተው ወሲባዊ ጥቃት እንደ ጦር ስልት አለያም ለበቀል መወጫነት እንደዋለ ተናግረዋል። 

አክለውም፤ ጥቃቱ ዘር ላይ ያተኮረ እንደሆነና ሰለባዎቹንና ማኅበረሰባቱን ለማዋረድም እንደዋለ አመላክተው፤ ለትግራይና ሌሎች ሥፍራዎችም የአዕምሮ ጤና እገዝ እንዲደረግ ለምክር ቤቱ ታዳሚ አምባሳደሮች አሳስበዋል። 

 

 


Share

Published

By Kassahun Seboqa Negewo

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service