አርጀንቲና ዛሬ ማለዳ ክሮኤሽያን 3 ለ 0 ረትታ ለዓለም ዋንጫ ፍፃሜ ግጥሚያ በቅታለች።
ግቦቹን ለአርጀንቲና ያስቆጠሩት ሊዮኔል ሚሲ በ34ኛዋ ደቂቃ የመጀመሪያዋን ግብ (በፍፁም ቅጣት ምት)፣ ሁሊያን አልቫሬዝ በ39ኛ እና 69ኛ ደቂቃዎች ሁለተኛ እና ሶስተኛ ግቦችን ከመረብ አኑሯል።

በ2018 የዓለም ዋንጫ ውድድር ለፍፃሜ ደርሶ ዋንጫውን በፈረንሳይ የተነጠቀው የክሮኤሽያ ቡድን ዛሬም እንደ 2018ቱ ለፍፃሜ ይበቃል የሚል የጠነከረ ተስፋን በደጋፊዎቹ ዘንድ ያሳደረ ቢሆንም በለስ ሳይቀናው በ3 ለ 0 ሽንፈት ተሰናባች ሆኗል።
የክሮኤሽያ ቡድን በመከላከል ላይ ያደላ ሲሆን፤ ለግብ አስጊ የነበረ ሙከራውን ከአንድ ጊዜ በላይ አላስቆጠረም።
ሽንፈቱ እንደ ደጋፊዎቹ ሁሉ ተስፈኛ የነበሩትን የተጫዋቾቹንም ልብ ሰብሯል።

የግማሽ ፍፃሜ ግጥሚያ ሠንጠረዥ
ፈረንሳይ እና ሞሮኮ (ሐሙስ ዲሴምበር 15 / ታሕሳስ 6) 6:00 am [AEDT]

