የፌዴራል መንግሥቱና የኦሮሞ ነፃነት ታጣቂዎች ድርድር ከወታደራዊ ወደ የፖለቲካ አመራር ተወካዮች ተሸጋግሯል

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በተገኙበት የሕዝብ ተወካዮች መደበኛ ስብሰባ ተካሔደ

SBS Amharic News Podcast World.jfif

Credit: SBS Amharic

በኢፌዴሪ ወታደራዊ አመራሮችና በኦሮሞ ነፃነት ታጣቂዎች ታንዛኒያ መዲና ዳሬሰላም የተጀመረው የሰላም ንግግር ወደ ሁለኛ ምዕራፍ ተሸጋግሮ በፖለቲካ አመራር ተወካዮች መካሔድ መጀመሩን ቅርብርት ያላቸው ምንጮች ገልጠዋል።

በመንግሥት በኩል አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን የጠቅላይ ሚንስትሩ ብሔራዊ ደህንነት አማካሪና የፍትሕ ሚኒስት ጌዲዮን ጢሞቴዎስ የሰላም ውይይቱን በተወካይነት ለማካሔድ ሕዳር 2 ዳሬሰላም መግባታቸው ተነግሯል።

በታካይነትም የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ባለስልጣናት ከታጣቂዎቹ አመራር አባላት ጋር መነጋገራቸው ተጠቁሟል።

የመጀመሪያው ውይይት የተጀመረው ጥቅምት 27 ቀን 2016 ሲሆን፤ ለውይይቱ ስኬት የአሜሪካ፣ የኢጋድ፣ ኬንያና ኖርዌይ መንግሥታት ተወካዮች ድጋፍ እየቸሩ መሆኑም ተመልክቷል።

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት

የኢፌዴሪ ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሶስተኝ ዓመት አራተኛ መደበኛ ስብሰባ በዛሬው ዕለት ተከናውኗል።

በሂደቱም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከሕዝብ ተወካዮች ለቀረቡላቸው ዘርፈ ብዙ ጥያቄዎች ምላሾችን ሰጥተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሰጧቸው ምላሾች ሰላምና ደሕንነት፣ የመከላከያ ሠራዊትና የኢትዮጵያ ሕልውና፣ የብዙኅን መገናኛ ዘገባዎችን፣ የልማት ሥራዎችን፣ የትምህርት፣ ምጣኔ ሃብት፣ ሙስናንና በክልሎች መካክል ያሉ የይገባኛል ወሰን ልዩነቶችን አንስተዋል።

በተለይም በትግራይና በአማራ ክልል ያለውን "አከራካሪ በሆኑ" አካባቢዎች ብለው ለጠሩት የይገባኛል ጥያቄ መፍቻ መንግሥታቸው ይዞት ያለው አማራጭ መፍትሔ ሕዝበ ውሳኔ እንደሆነ አመላክተው "ሌላ የመፍትሔ ሃሳብ ካለ የፌዴራል መንግሥት በደስታ" እንደሚቀበል ተናግረዋል።

አክለውም፤ የአማራና ኦሮሞ ሕዝቦች "ፈለጉም አልፈለጉም በሰላም ለመኖር ያላቸው ምርጫ አንድ ብቻ ነው፤ይህም የአንድ አባት ልጆች ፣ የአንድ ሀገር ዜጎች ወንድማማቾች መሆናቸውን አውቀው በሰላም በተከባበረ አብሮ መኖር በሚያስችል ማንነት መጉዋዝ ብቻ ነው" ብለዋል።







Share

Published

By Stringer Report
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service