Watch FIFA World Cup 2026™

LIVE, FREE and EXCLUSIVE

የኤፌዴሪ ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ በአብላጫ ድምፅ ይሁንታን ቸረ

የቀድሞው የአማራ ክልል ፕሬዚደንት አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ለአማራ ክልል ችግር ፖለቲካዊ እንጂ ወታደራዊ መፍትሔ እንደማያሻው አሳሰቡ።

HPR.jpg

Credit: HPR

የኢፌዴሪ ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ነሐሴ 8 ከቀትር በኋላ በአካሔደው አስቸኳይ ስብሰባ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ፀድቆ በተመራለት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አጀንዳ ላይ ተነጋግሮ በ332 የድጋፍ ድምፅ ይሁንታውን ቸሯል።

በድምፅ አሰጣጡ ሥነ ሥርዓት ወቅትም 16 ተቃውሞና 12 ድምፀ ተዐቅቦ ተመዝግቧል።

በዕለቱ በአስቸኳይ ስብሰባው ላይ 330 የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ታድመዋል።

በስብሰባው ላይ የቀድሞው የአማራ ክልል ፕሬዚደንት አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ባሰሙት ንግግር እሳቸው የሚወክሉት ጥቂት ፅንፈኞችን ሳይሆን የአማራን ሕዝብ መሆኑን አስገንዝበው "የአማራ ሕዝብ ችግር ፖለቲካዊ ችግር ነው። ለፖለቲካዊ ችግር ፖለቲካዊ መፍትሔ እንጂ ወታደራዊ መፍትሔ አያሻውም" ብለዋል።

አክለውም "የመከላከያ ሠራዊቱ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ወደ ካምፑ ይመለስ፤ ሁሉንም የአማራ ኃይሎች ያቀፈ ጊዜያዊ አስተዳደር ይቋቋም" ሲሉ ጠይቀዋል።


1 min read

Published

Updated

By Stringer Report

Source: SBS


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now