የኤፌዴሪ ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ በአብላጫ ድምፅ ይሁንታን ቸረ

የቀድሞው የአማራ ክልል ፕሬዚደንት አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ለአማራ ክልል ችግር ፖለቲካዊ እንጂ ወታደራዊ መፍትሔ እንደማያሻው አሳሰቡ።

HPR.jpg

Credit: HPR

የኢፌዴሪ ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ነሐሴ 8 ከቀትር በኋላ በአካሔደው አስቸኳይ ስብሰባ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ፀድቆ በተመራለት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አጀንዳ ላይ ተነጋግሮ በ332 የድጋፍ ድምፅ ይሁንታውን ቸሯል።

በድምፅ አሰጣጡ ሥነ ሥርዓት ወቅትም 16 ተቃውሞና 12 ድምፀ ተዐቅቦ ተመዝግቧል።

በዕለቱ በአስቸኳይ ስብሰባው ላይ 330 የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ታድመዋል።

በስብሰባው ላይ የቀድሞው የአማራ ክልል ፕሬዚደንት አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ባሰሙት ንግግር እሳቸው የሚወክሉት ጥቂት ፅንፈኞችን ሳይሆን የአማራን ሕዝብ መሆኑን አስገንዝበው "የአማራ ሕዝብ ችግር ፖለቲካዊ ችግር ነው። ለፖለቲካዊ ችግር ፖለቲካዊ መፍትሔ እንጂ ወታደራዊ መፍትሔ አያሻውም" ብለዋል።

አክለውም "የመከላከያ ሠራዊቱ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ወደ ካምፑ ይመለስ፤ ሁሉንም የአማራ ኃይሎች ያቀፈ ጊዜያዊ አስተዳደር ይቋቋም" ሲሉ ጠይቀዋል።




Share

Published

Updated

By Stringer Report
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service
የኤፌዴሪ ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ በአብላጫ ድምፅ ይሁንታን ቸረ | SBS Amharic